ሐኪም ሆይ! ይህ ገንዘብ ለምለምና ጣፋጭ ነው።

ሐኪም ሆይ! ይህ ገንዘብ ለምለምና ጣፋጭ ነው።

ከሐኪም ቢን ሒዛም -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላችውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህን መልክተኛ - የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና - ጠየቅኳቸውና ሰጡኝ። ድጋሚ ጠየቅኳቸውና ሰጡኝ። ከዚያም እንዲህ አሉኝ: "ሐኪም ሆይ! ይህ ገንዘብ ለምለምና ጣፋጭ ነው። ይህንን ገንዘብ ነፍሱ እንደተከበረች (ሳይለምን) የወሰደው ሰው ለርሱ ይባረክለታል። ነፍሱን (ለልመና) በማውጣት የወሰደው ሰው ለርሱ አይባረክለትም። እርሱም እየበላ እንደማይጠግብ ሰው ምሳሌ ነው። ከላይ ያለች እጅ ከታች ካለች እጅ የተሻለች ናት።" ሐኪምም እንዲህ አለ: "የአላህ መልክተኛ ሆይ! በእውነት በላከዎ ጌታ እምላለሁ! ዱንያን እስከምለያይ ድረስ ከዚህ በኋላ ማንንም አልለምንም። አልኩኝ።"» አቡ በክር ሐኪምን ስጦታ ሊሰጠው ይጠራው ነበር። አንዳችም ከርሱ አልቀበልም ብሎ እምቢ አለ። ከዚያም ዑመር ሊሰጠው ጠራው። ከርሱ ከመቀበልም እምቢ አለ። ዑመርም እንዲህ አለ: "እናንተ ሙስሊሞች ሆይ! እኔ ለሐኪም ከምርኮ ገንዘብ አላህ ድርሻው ያደረገለትን ሐቁን አቀረብኩለት። እርሱ ግን እምቢ አለ።" ሐኪም እስኪሞት ድረስ ከነቢዩ - የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና - ከተቀበለ በኋላ የአንድንም ሰው ገንዘብ በመውሰድ አላጎደለም ነበር።»

[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]

الشرح

ሐኪም ቢን ሒዛም -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላችውና- ነቢዩን - የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና - የዱንያ መጣቀሚያ የምትሆንን ጠየቀና ሰጡት። ድጋሚ ጠየቃቸውና ሰጡት። ከዚያም ነቢዩ - የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ አሉት: "ሐኪም ሆይ! ይህ ገንዘብ የሚጓጓለትና የሚከጀል ነው። ይህንን ገንዘብ ሳይለምን ነፍሱ እጅግ ሳትጓጓና ችክ ሳይል ያገኘው ሰው ለርሱ ይባረክለታል። ነፍሱን ለሰዎች በማቅረብና በመከጀል ያገኘው ሰው ለርሱ አይባረክለትም። እርሱም እየበላ እንደማይጠግብ ሰው ምሳሌ ነው። ከላይ ያለች ሰጪ እጅ ከታች ካለች ከምትለምን እጅ አላህ ዘንድ የተሻለች ናት።" ሐኪምም እንዲህ አለ: "የአላህ መልክተኛ ሆይ! በእውነት በላከዎ ጌታ እምላለሁ! ዱንያን እስከምለያይ ድረስ (አሁን ከሰጡኝ) ከርሶ ገንዘብ በኋላ የማንንም ገንዘብ ለምኜ አላጎድልም።" አልኩኝ። የአላህ መልክተኛ ምትክ አቡ በክር - አላህ መልካም ስራውን ይውደድለትና - ሐኪምን ስጦታ ሊሰጠው ይጠራው ነበር። አንዳችም ከርሱ አልቀበልም ብሎ እምቢ አለ። ከዚያም የአማኞች መሪ ዑመርም - አላህ መልካም ስራውን ይውደድለትና - ሊሰጠው ጠራው። ከርሱ ከመቀበልም እምቢ አለ። ዑመርም እንዲህ አለ: "እናንተ ሙስሊሞች ሆይ! እኔ ለሐኪም ከከሃዲያን ጋር ምንም ጦርነትና ጂሃድ ሳይደረግ ከተሰበሰበ ከምርኮ ገንዘብ አላህ ድርሻው ያደረገለትን ሐቁን አቀረብኩለት። እርሱ ግን እምቢ አለ።" ሐኪም እስኪሞት ድረስም ከነቢዩ - የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና - ከተቀበለ በኋላ የአንድንም ሰው ገንዘብ በመውሰድ አላጎደለም ነበር።

فوائد الحديث

በተደነገገ መንገድ ገንዘብን መውሰድና ማጠራቀም ዱንያን ቸል ከማለት (ከዙህድ) ጋር አይጋጭም። (ዙህድ) ዱንያን ቸል ማለት ነፍስን ማክበርና ቀልብን በገንዘብ አለማንጠልጠል ማለት ነውና።

የነቢዩ - የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና - ቸርነት የላቀ መሆኑን መገለፁን እና መቼም ድህነትን እንደማይፈራ ሰው አሰጣጥ እንደሚሰጡ እንመለከታለን።

እገዛን በምናቀርብ ወቅት ለወንድሞች የሚጠቅማቸውን ነገር ለመምከር መጣርና ምክርን መለገስ ይገባል። ምክንያቱም ነፍስ በመልካም ንግግር ለመጠቀም የተዘጋጀች ትሆናለችና።

ሰዎችን ከመለመን መጠበቅና ከልመና መሸሽ እንደሚገባ በተለይ አስፈላጊ ባልሆነበት ወቅት ከመለመን መራቅ እንደሚገባ እንረዳለን።

ከዚህ ሐዲሥ ለገንዘብ መጓጓትና ልመናን ማብዛት መወገዙን እንረዳለን።

ለማኝ ችክ ብሎ ከለመነ ባዶ እጁን መመለስ፣ አለመስጠት ይልቁንም መምከር፣ ጥብቅ ሰው እንዲሆንና ገንዘብ ለማግኘት ጉጉ መሆን እንደሌለበት ማዘዝ ችግር የለውም።

አንድም ሰው ከሙስሊሙ ግምጃ ቤት መሪው ካልሰጠው በቀር መውሰድ አይገባውም። ምርኮ ከመከፋፈሉ በፊትም መውሰድ ተገቢ አይደለም።

አስፈላጊ ሲሆን መለመን እንደሚፈቀድ እንረዳለን።

ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: "ከዚህ ሐዲሥ እንደምንረዳው መሪ የሆነ ሰው ከርሱ ፈልጎ የመጣን ሰው መለመኑ ስለሚያስከትልበት ጉዳት ከሰጠው በኋላ ነው ሊያብራራ የሚገባው። ይህም ምክሩ ተሰሚነት እንዲኖራት ነው። ሳይሰጠው መምከሩ ፍላጎቱን ለመከልከል የተጠቀመው ዘዴ ተደርጎ እንዲወሰድ ሊያደርግበት ይችላልና።"

የሐኪም -አላህ መልካም ስራውን ይውደድለትና - ደረጃ እንረዳለን። ለአላህና ለአላህ መልክተኛ - የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና - የገባውን ቃል እንደተወጣም እንመለከታለን።

ኢስሓቅ ቢን ራሀዊየህ እንዲህ ብለዋል: "ሐኪም -አላህ መልካም ስራውን ይውደድለትና - በሚሞት ጊዜ ከቁረይሾች እጅግ የበዛ ገንዘብ ያለው ሆኖ ነው።"

التصنيفات

ዱንያን ከመውደድ ማውገዝ