አንዳችሁ ከሶስት ድንጋይ ባነሰ ኢስቲንጃእ እንዳያደርግ (እንዳያጥራራ)።

አንዳችሁ ከሶስት ድንጋይ ባነሰ ኢስቲንጃእ እንዳያደርግ (እንዳያጥራራ)።

ከሰልማን (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «አጋርያኖች ለኛ እንዲህ አሉን: "እኔ እንደማየው ባልደረባችሁ እንዴት እንደምትፀዳዱ ሳይቀር ያስተምራችኋል አይደል?" እኔም እንዲህ በማለት መለስኩላቸው አዎ እርሳቸው እያንዳንዳችን በቀኝ እጁ ከመጥራራት (ኢስቲንጃእ ከማድረግ) ወይም ወደ ቂብላ አቅጣጫ ዞሮ ከመፀዳዳት ከልክለውናል። በፍግና በአጥንት ከመፀዳዳት (ኢስቲንጃእ ከማድረግም) ከልክለውናል። እንዲህም ብለውናል "አንዳችሁ ከሶስት ድንጋይ ባነሰ ኢስቲንጃእ እንዳያደርግ (እንዳያጥራራ)።"»

[ሶሒሕ ነው።] [ሙስሊም ዘግበውታል።]

الشرح

ሰልማን አልፋሪሲይ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንዲህ አሉ: አጋርያኖች በኛ ላይ ለማሾፍ እንዲህ አሉን: ነቢያችሁ ከሽንት ወይም ከሰገራ እንዴት እንደምትፀዳዱ ሳይቀር ሁሉንም ያስተምራችኋል አይደል? ሰልማንም እንዲህ በማለት መለሰ: "አዎ የመፀዳዳትን ስነስርዓት አስተምረውናል። ከዚህም መካከል ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ከተፀዳዳን በኋላ ቀኝ እጅን ከነጃሳ ለመጠበቅና ለቀኝ እጅ ክብር በቀኝ እጅ ኢስቲንጃእ ከማድረግ ወይም ሽንታችንንና ሰገራችንን በምንፀዳዳበት ወቅት ወደ ከዕባ ዞረን ከመፀዳዳት ከልክለውናል። በእንስሶች ፍግና አጥንት ከማደራረቅ ከልክለውናል። ዉዱእ ያጠፋና ተፀዳድቶ የሚያደራርቅ ሰውም ከሶስት ድንጋይ ባነሰ እንዳያደራርቅ ከልክለዋል።

فوائد الحديث

የእስልምና ሸሪዓ የሰው ልጅ የሚያስፈልገውን ሁሉ ያካተተና ያቀፈ መሆኑን ተገልጿል።

የተወሰኑ የመፀዳዳትና የኢስቲንጃእ አዳቦች ተገልፀዋል።

በመሽናት ወይም ሰገራን በማውጣት ወቅት ወደ ቂብላ መዞር ክልክል መሆኑን እንረዳለን። ይህም "ከለከሉን" ከሚለው ቃል ነው የምንረዳው። ክልከላ በመሰረቱ ሐራምነትን ነው የሚጠቁመውና።

ቀኝ እጅን ለማክበር በቀኝ እጅ ኢስቲንጃእም (በውሃ መታጠብ) ሆነ ወይም ማደራረቅ መከልከሉን እንረዳለን።

ቀኝ እጅ ከግራ እጅ እንደሚበልጥ እንረዳለን። ይኸውም ግራ እጅ ነጃሳንና ቆሻሻን ለማስወገድ ነው የምንጠቀምበት። ቀኝ እጅን ግን ከዛ ውጪ ላለ ነው የምንጠቀምበት።

ነጃሳን አነሰችም በዛችም በውሃ ወይም በድንጋይ ማስወገድ ግዴታ መሆኑን እንረዳለን።

ከሶስት ድንጋይ ባነሰ ማደራረቅ መከልከሉን እንረዳለን። ይኸውም በአብዛኛው ከሶስት ድንጋይ ያነሰ ስለማያጠራ ነው።

ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ድንጋይን የጠቀሱት በአብዛኛው የሚጠቀሙት እርሱን ስለሆነ እንጂ የታለመውን ማጥራትና ማፅዳት ሊያስገኝልን የሚችል ነገር ሁሉ መጠቀም ይፈቀዳል። እንዲህ የሆነ ነገር ደግሞ ከርሱ ውጪ ባለ በሌላ ነገር አይፈቀድም የሚልን አያስገነዝብም።

ማደራረቅን በጎዶሎ ቁጥር ማጠናቀቅ እንደሚወደድ እንረዳለን። በአራት ድንጋይ ከጠራለት አምስተኛን መጨመሩ ይወደዳል። ይህም ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - (ያደራረቀ ሰው ማደራረቁን በጎዶሎ ቁጥር ያጠናቅቅ) ስላሉ ነው።

በፍግ ኢስቲጅማር ማድረግ መከልከሉን እንረዳለን። ይህም ወይ ነጃሳ ስለሆነ ነው ወይም የጂን እንስሶች ቀለብ ስለሆነ ነው።

በአጥንት ኢስቲጅማር ማድረግ መከልከሉን እንረዳለን። ይህም ወይ ነጃሳ ስለሆነ ነው። ወይም የጂኖች ምግብ ስለሆነ ነው።

التصنيفات

የመፀዳጃ ቤት ስነ-ስርዓት