አላህ እንዲህ ብሏል: ‹ሁሉም የአደም ልጅ ስራ ለርሱ ነው ፆም ሲቀር፤ ፆም ለኔ ነው። በርሱ የምመነዳውም እኔው ነኝ።

አላህ እንዲህ ብሏል: ‹ሁሉም የአደም ልጅ ስራ ለርሱ ነው ፆም ሲቀር፤ ፆም ለኔ ነው። በርሱ የምመነዳውም እኔው ነኝ።

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል: "አላህ እንዲህ ብሏል: ‹ሁሉም የአደም ልጅ ስራ ለርሱ ነው ፆም ሲቀር፤ ፆም ለኔ ነው። በርሱ የምመነዳውም እኔው ነኝ።› ፆም ጋሻ ነው። አንዳችሁ የፆም ቀኑ የሆነ ጊዜ ፀያፍ ቃልንም አይናገር አይጩህም። አንድ ሰው ከተሰዳደበው ወይም ከተጋደለው እኔ ፆመኛ ሰው ነኝ ይበል። የሙሐመድ ነፍስ በእጁ በሆነው ጌታ እምላለሁ! የፆመኛ ሰው የአፍ ጠረን አላህ ዘንድ ከሚስክ ሽታ የበለጠ ታውዳለች። ፆመኛ የሚደስትባቸው ሁለት ደስታ አሉት። ሲያፈጥርም ይደሰታል። ጌታውን የተገናኘ ጊዜም በመፆሙ ይደሰታል።"»

[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪ ዘግበውታል። - ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]

الشرح

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና አላህ በሐዲሠል ቁድስ እንዲህ እንደሚል ተናገሩ:- ሁሉም የአደም ልጅ መልካም ስራ ከአስር እስከ ሰባት መቶ እጥፍ ይነባበራል ፆም ሲቀር፤ ፆም ይዩልኝ የማይገባበት ስራ ነውና ለኔ ነው። እኔ ነኝ በርሱ የምመነዳው፤ የምንዳውን መጠንም ይሁን የአጅሩን መነባበር መጠን በማወቅ የተነጠልኩት እኔ ብቻ ነኝ። ቀጥለው (ፆም ጋሻ ነው) አሉ። ከእሳት የሚጠብቅ ጋሻ፣ መሸሸጊያና መጠበቂያ ነው። ፆም ወንጀል ላይ ከመውደቅ ስሜትን የሚያቅብ ነው። እሳት በስሜቶች የተከበበች ናትና። (አንዳችሁ የፆም ቀኑ የሆነ ጊዜ ፀያፍ ቃልን አይናገር) በግንኙነት ጉዳይም ይሁን ወደ ግንኙነት በሚያነሳሱ ነገሮች፤ በጥቅሉ የትኛውንም ፀያፍ ንግግር አይናገር። (አይጩህም።) በክርክርና በጩኸት አይናገር። በረመዷን (አንድ ሰው ከተሰዳደበው ወይም ከተጋደለው) ከርሱ ሊቆጠብ ይከጀላልና እኔ ፆመኛ ሰው ነኝ ይበል። ሰውዬው ካልተጋደልኩ ብሎ ከደረቀ ሰው ሊያጠቃው ሲመጣ እንደሚያደርገው በቀላል መልኩ ይከላከለው። ቀጥለው ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በፆም ምክንያት የተለወጠ የፆመኛ አፍ ጠረን መዓዛው የትንሳኤ ቀን አላህ ዘንድ ‐እናንተ ዘንድ ካለው የሚስክ መአዛ የበለጠ‐ እንደሚያውድ፤ ምንዳው ደሞ በጁመዓና በዚክር መቀማመጥ ወቅት መቀባቱ ተወዳጅ ከሆነው ሚስክ የበለጠ ምንዳም እንደሚያስገኝ ነፍሳቸው በእጁ በሆነው ጌታ ምለው ተናገሩ። ፆመኛ የሚደሰትባቸው ሁለት ደስታዎች አሉት: በሚያፈጥር ወቅት ማፍጠሩ ተፈቅዶለት አፍጥሮ ረሃቡና ጥሙ በመወገዱ፣ ፆሙ በመሙላቱና አምልኮው በመጠናቀቁ፣ በጌታው ማቅለያና ለቀጣይ ፆሙ ማገዣ በመቅመሱ ይደሰታል። (ጌታውን የተገናኘ ጊዜም በፆሙ ይደሰታል።) በምንዳውና በክፍያው ይደሰታል።

فوائد الحديث

የፆም ትሩፋትን እንረዳለን። ፆም በዱንያ ፆመኛውን ከስሜት ይጠብቀዋል። በመጪው አለም ደግሞ ከእሳት ቅጣት ይጠብቀዋል።

ከፆም ስነ ስርዓቶች መካከል ፀያፍ ንግግርና ጫጫታን መተው፤ ሰው በሚያውከን ሰአት መታገስ፣ የነርሱን መጥፎ ተግባር አፀፋ በትእግስትና በመልካም መመለስ ይጠቀሳሉ።

ፆመኛ ወይም አንድ ባሪያ አምልኮው በመጠናቀቁና በመሙላቱ ምክንያት መደሰቱ በመጪው አለም ከሚያገኘው ምንዳ ምንም አያጎድልበትም።

የተሟላ ደስታ የሚገኘው አላህን በመገናኘት ነው። ይህም ታጋሾችና ፆመኞች ምንዳቸውን ያለቁጥር በሚመነዱበት ወቅት ማለት ነው።

አስፈላጊና ጠቃሚ ሆኖ በሚገኝበት ወቅት አምልኮ ላይ መሆንን ለሰዎች ማሳወቅ ይዩልኝ አያስብልም። (እኔ ፆመኛ) ነኝ ይበል ስላሉ።

አንድ ሰው የተሟላ ፆም ፆመ የሚባለው አካላቱ ወንጀል ከመፈፀም የቆጠበ ጊዜ፤ ምላሱ ከውሸት፣ ከፀያፍ ንግግርና የቅጥፈት ንግግር ከመናገር ዝም ያለ ጊዜ፤ ሆዱም ከምግብና መጠጥ የተከለከለ ጊዜ ነው።

ከጫጫታ፣ ከክርክርና ከመጮህ በአፅንዖት መከልከሉ ለፆመኛ ይበልጥ የበረታ ይሁን እንጂ ፆመኛ ያልሆነም ሰው ከነዚህ ተግባራት ተከልክሏል።

ይህ ሐዲሥ ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ከጌታቸው ከሚያወሩት ሐዲሥ መካከል ነው። "ሐዲሠል ቁድስ" ወይም "ሐዲሠል ኢላሂይ" በመባልም ይጠራል። ይህም ቃሉም መልዕክቱም ከአላህ ቢሆንም ቁርአን ከሌሎች የተለየበት የሆኑ ‐ማለትም ማንበቡ ብቻ አምልኮ መሆኑ፣ ለማንበብ ዉዱእ ማስፈለጉ፣ አላህ የርሱን አምሳያ አምጡ ብሎ መገዳደሩ፣ ተአምራዊነትና ሌሎችም‐ የቁርአን መገለጫዎች የሌሉት ነው።

التصنيفات

የጾም ትሩፋት