የወንድሙን ክብር በመንካት ወይም በአንዳች ነገር ወንድሙን የበደለ ሰው ዲናርና ዲርሃም የሌለበት ቀን ከመምጣቱ በፊት ዛሬ ከራሱ ላይ በደሉን ያስነሳ።

የወንድሙን ክብር በመንካት ወይም በአንዳች ነገር ወንድሙን የበደለ ሰው ዲናርና ዲርሃም የሌለበት ቀን ከመምጣቱ በፊት ዛሬ ከራሱ ላይ በደሉን ያስነሳ።

ከአቡ ሁረይራ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ ብለዋል: "የወንድሙን ክብር በመንካት ወይም በአንዳች ነገር ወንድሙን የበደለ ሰው ዲናርና ዲርሃም የሌለበት ቀን ከመምጣቱ በፊት ዛሬ ከራሱ ላይ በደሉን ያስነሳ። (የትንሳኤ ቀን) መልካም ስራ ካለው በበደሉ ልክ ይቀነስበታል። ለርሱ መልካም ስራ ከሌለው ከበደለው ባልደረባው ወንጀሎች ተወስደው እርሱ ላይ ይደረጋሉ።"»

[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪ ዘግበውታል።]

الشرح

ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ሙስሊም ወንድሙን በክብሩ ወይም በገንዘቡ ወይም በደሙ የበደለ ሰው ነፍሱን ለማዳን ለበደለው ሰው የሚሰጠው የወርቅ ዲናርም ሆነ የብር ዲርሃም የማይጠቅምበት የትንሳኤ ቀን ከመምጣቱ በፊት በዱንያ ውስጥ እስካለ ድረስ የተበዳዩን ይቅርታ እንዲጠይቅ አዘዙ። የትንሳኤ ቀን ፍርድ የሚሰጠው በመልካም ስራዎችና ሀጢአቶች ነውና። ተበዳዩ ከበዳዩ መልካም ስራዎች ቀንሶ የተበደለውን ያህል መልካም ስራዎችን ይወስዳል። በዳዩ መልካም ስራዎች ከሌሉት በበደሉ ልክ ከተበዳዩ ወንጀሎች ተወስደው በበዳዩ ላይ ይደረጋሉ።

فوائد الحديث

ከበደልና ወሰን ከመተላለፍ በመራቅ ላይ መጣር እንደሚገባ እንረዳለን።

ከሰው ሐቆች ጋር የተያያዙን ነገሮች ከጫንቃችን ላይ ለማፅዳት በመቻኮል ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።

መልካም ስራዎች ሰዎችን በመበደልና በማወክ ይበላሻሉም ፍሬ አልባም ይሆናሉ።

የሰዎች ሐቅ ወደ ባለቤቱ በመመለስ ካልሆነ በቀር አላህ የሚምረው ጉዳይ አይደለም።

ዲናርና ዲርሃም በዱንያ ውስጥ ጥቅምን ለማስገኘት የምንዳረስባቸው መንገዶች ናቸው። በመጪው አለም ግን ለክፍያ ጥቅም ላይ የሚውሉት መልካም ስራዎችና ሀጢአቶች ብቻ ናቸው።

አንዳንድ ዑለሞች ክብርን በመንካት ጉዳይ እንዲህ ብለዋል: "ተበዳዩ ክብሩ እንደተነካ የማያውቅ ከሆነ ማሳወቁ አስፈላጊ አይደለም። ለምሳሌ በአንድ ስፍራ ቢሰድበውና ስለስድቡ ተውበት ቢያደርግ የግድ ሰድቤሃለሁ ብሎ ማሳወቅ አያስፈልግም። ይልቁንም ለርሱ ምህረትን ይጠይቅለታል። ዱዓም ያደርግለታል። ይሰድበው የነበረበት ስፍራ ላይም በመልካም ያወሳዋል። በዚህም የስድቡ ወንጀል ይነሳለታል።"

التصنيفات

የመጨረሻው ህይወት