አንድ ሰውዬ ነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ስለ ትንሳኤ እለት ጠየቃቸው። "ትንሳኤ መቼ ነው?" አላቸው። እርሳቸውም "ለርሷ ምን አዘጋጅተሀል?" አሉት።

አንድ ሰውዬ ነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ስለ ትንሳኤ እለት ጠየቃቸው። "ትንሳኤ መቼ ነው?" አላቸው። እርሳቸውም "ለርሷ ምን አዘጋጅተሀል?" አሉት።

ከአነስ (ረዲየላሁ ዐንሁ) -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «አንድ ሰውዬ ነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ስለ ትንሳኤ እለት ጠየቃቸው። "ትንሳኤ መቼ ነው?" አላቸው። እርሳቸውም "ለርሷ ምን አዘጋጅተሀል?" አሉት። እርሱም "እኔ አላህና መልክተኛውን (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከመውደዴ ውጭ ምንም ነገር አላዘጋጀሁም።" አለ። እርሳቸውም "አንተ ከወደድካቸው ጋር ነህ።" አሉት። አነስም እንዲህ አሉ፦ "በዚህ "አንተ ከወደድካቸው ጋር ነህ።" በሚለው የነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ንግግር እንደተደሰትነው በምንም አልተደሰትንም።" ቀጥሎም (አነስ) እንዲህ አሉ: "እኔ ነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና)፣ አቡበከርንና ዑመርን እወዳለሁ። እነርሱ የሰሩትን አምሳያ ባልሰራ እንኳ እነርሱን በመውደዴ ከነርሱ ጋር መሆንን ተስፋ አደርጋለሁ።"»

[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]

الشرح

አንድ የገጠር ሰው ነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ትንሳኤ ስለምትከሰትበት ወቅት ጠየቃቸው። ነቢዩም (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ለርሱ: ለርሷ ከመልካም ስራ ምን አዘጋጅተህላታል? አሉት። ጠያቂውም: እኔ አላህና መልክተኛውን እወዳለሁ እንጂ ትልቅ ስራ አላዘጋጀሁላትም አለ። ከዚህ በቀር የቀልብም፣ የአካልም ሆነ የገንዘብ አምልኮ አላወሳም። እነዚህ ሁሉ ውዴታን ተከትሎ የሚመጡ ቅርንጫፎች ናቸውና። ለመልካም ስራ የሚያነሳሳውም እውነተኛ ውዴታ ስለሆነ ነው። ነቢዩም (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ለርሱ: አንተ ጀነት ውስጥ ከወደድካቸው ጋር ነህ አሉት። የነቢዩም (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሶሐቦች በዚህ ብስራት ከፍተኛ ደስታን ተደሰቱ። አነስም (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ቀጥሎ ስራው እንደነርሱ አምሳያ ባይሆንም እንኳ ነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና)፣ አቡበከርንና ዑመርን ስለሚወድ ከነርሱ ጋር መሆንንም ተስፋ እንደሚያደርግ ተናገረ።

فوائد الحديث

የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ለጠያቂ መልስ ሲሰጡ የተጠቀሙትን ጥበብ እንረዳለን። ለጠያቂው አንገብጋቢውንና የሚያድነው የሆነውን ጉዳይ ጠቆሙት። እርሱም: በሚጠቅም መልካም ስራ ለመጪው አለም መዘጋጀት ነው።

ሰው አላህን ለመገናኘት ተዘጋጅቶና ተሰናድቶ እንዲኖር አላህ የትንሳኤን ቀን እውቀት ከባሮቹ ላይ ደበቀው።

አላህን፣ መልክተኞችን፣ አማኝ የሆኑ ደጋጎችን የመውደድን ትሩፋትና አጋርያንን ከመውደድ መጠንቀቅ እንደሚገባ እንረዳለን።

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና): አንተ ከወደድካቸው ጋር ነህ ማለታቸው በደረጃና በማዕረግ እኩል መሆንን አይጠቁምም። ይልቁኑም የተፈለገው ምንም ቢራራቁ ራሱ አንዱ ሌላውን መመልከት በሚችልበት መልኩ በጀነት ውስጥ እንደሚሆኑ ነው።

ሙስሊምን እጅግ በሚጠቅመውና በሚበጀው ጉዳይ እንዲጠመድና ስለማይጠቅመው ነገር ከመጠየቅ እንዲተው መጠቆም እንደሚገባ እንረዳለን።

التصنيفات

በመጨረሻው ቀን ማመን, የቀልብ ተግባራት