‹አንድ አማኝ የትንሳኤ ቀን ወደ ጌታው ይቀርባል። በርሱ ላይ መሸፈኛውን አኑሮበት ወንጀሎቹን እንዲያምን ያደርገዋል።

‹አንድ አማኝ የትንሳኤ ቀን ወደ ጌታው ይቀርባል። በርሱ ላይ መሸፈኛውን አኑሮበት ወንጀሎቹን እንዲያምን ያደርገዋል።

ከሶፍዋን ቢን ሙሕሪዝ እንደተላለፈው እንዲህ አለ: «አንድ ሰውዬ ለኢብኑ ዑመር (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንዲህ አለ: "የአላህን መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ስለ መመሳጠር ሲናገሩ የሰማሀው ነገር አለን?" እርሱም አለ: "እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ: ‹አንድ አማኝ የትንሳኤ ቀን ወደ ጌታው ይቀርባል። በርሱ ላይ መሸፈኛውን አኑሮበት ወንጀሎቹን እንዲያምን ያደርገዋል። 'አወቅከውን?' ይለዋል። እርሱም 'ጌታዬ አውቄዋለሁ።' ይላል። አላህም 'እኔ በዱንያ ውስጥ ባንተ ላይ ሸፍኛት ነበር። ዛሬ ደግሞ ላንተ እምርሃለሁ።' ይለዋል። የመልካም ስራ መጽሐፉም ይሰጠዋል። ከሀዲዎችና ሙናፊቆች ግን በፍጡራን መካከል ይጠሩና 'እነዚህ በአላህ ላይ ያስተባበሉ ናቸው' ይባላሉ።›"»

[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]

الشرح

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና አላህ አንድ አማኝ ባሪያውን የትንሳኤ ቀን እንደሚመሳጠረው እንዲህ በማለት ተናገሩ: የትንሳኤ ቀን አማኝ የሆነ ሰው ወደ ጌታው ይቀርባል። ከርሱ ውጪ አንድም ሰው ምስጢሩን እንዳያውቅበትም ከቆሙ ሰዎች ይከልለዋል። እንዲህም ይለዋል: "እንዲህ እንዲህ ... ወንጀልህን አወቅከው?" እያለ በባሪያውና በጌታው መካከል የሰራውን ወንጀሎች እንዲያረጋግጥ ያደርገዋል። እርሱም "አዎ ጌታዬ" ይላል። አማኙ የደነገጠና የፈራ ጊዜም አላህ ሱብሓነሁ እንዲህ ይለዋል: "ምድር ላይ ላንተ ሸፍኜልሃለሁ። ዛሬ ደግሞ ላንተ እምርሃለሁ።" የመልካም ስራ መጽሐፉም ይሰጠዋል። ከሀዲና ሙናፊቅ ግን በፍጡራን መካከል እየተጠሩ እነዚህ በጌታቸው ላይ የዋሹ ናቸው። አዋጅ! የአላህ እርግማን በበዳዮች ላይ ይሁን ይባላሉ።

فوائد الحديث

አላህ ለአማኞች በዱንያም ሆነ በመጪው አለም በመሸፈኑ እዝነቱንና ችሮታውን እንረዳለን።

በተቻለ መጠን የአማኞችን ነውር በመሸፈን ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።

የባሮችን ስራ ባጠቃላይ የባሮች ጌታ ይጠብቃቸዋል። መልካምን ያገኘ ሰው አላህን ያመስግን። ከዚህ ውጪ ያገኘ ሰው ከነፍሱ በቀር ማንንም አይውቀስ። የርሱ ጉዳይም በአላህ መሻት ስር ነው።

ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: «አጠቃላይ በዚህ ዙሪያ የመጡ ሐዲሦች የሚጠቁሙት የትንሳኤ ቀን ወንጀለኛ አማኞች በሁለት እንደሚከፈሉ ነው: አንደኛው: ወንጀሉ በርሱና በጌታው መካከል የሆነ ነው። የኢብኑ ዑመር ሐዲስ ይህኛው የወንጀለኛ ክፍል ራሱ ሁለት አይነት እንደሆነ ይጠቁማል: አንደኛው አይነት ወንጀሉ በዱንያ የተሸሸገችለት ነው። ይህም ከሐዲሡ ግልፅ ቃል እንደምንረዳው የትንሳኤ ቀን አላህ ወንጀሉን ይሸፍንለታል። ሌላኛው አይነት ደግሞ ወንጀሉን በይፋ የሚሰራ ሰው ነው። ይህም ከሐዲሡ በተዘዋዋሪ እንደምንረዳው ከዚህ በተቃራኒ ወንጀሉ እንደማይሸሸግለት ነው። ሁለተኛው ክፍል: ወንጀሉ በርሱና በሰዎች መካከል የሆነ ነው። እነዚህም ሁለት አይነት ናቸው: አንደኛው አይነት: ወንጀላቸው ከመልካም ስራቸው ያመዘነችባቸው ናቸው። እነዚህ እሳት ይገቡና ከዚያም በምልጃ ከእሳት ይወጣሉ። ሌላኛው አይነት ደግሞ: መልካም ስራቸው ከመጥፎ ስራቸው ጋር እኩል የሆነባቸው ናቸው። እነዚህም በመካከላቸው በሰሩት በደል እስኪፈረድባቸው ድረስ ጀነት አይገቡም።»

التصنيفات

በመጨረሻው ቀን ማመን