አላህ ግዴታ ያደረገው ሲተገበር እንደሚወደው፤ ያግራውም ሲተገበር ይወዳል።

አላህ ግዴታ ያደረገው ሲተገበር እንደሚወደው፤ ያግራውም ሲተገበር ይወዳል።

ኢብኑ ዐባስ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንዲህ አሉ: የአላህ መልክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ አሉ፦ "አላህ ግዴታ ያደረገው ሲተገበር እንደሚወደው፤ ያግራውም ሲተገበር ይወዳል።"

[ሶሒሕ ነው።] [ኢብኑ ሒባን ዘግበውታል።]

الشرح

ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን አላህ አምልኮና ህግጋቶቹን በማቅለል የደነገጋቸው ማግራሪያዎች ሲተገበሩ እንደሚወድ ተናገሩ። እንዲሁም አቅመ አዳምና ጤነኛ የሆኑ ሰዎች በተቸገሩ ሰዓት የደነገገላቸውን ማቅለያዎች ለምሳሌ፦ ጉዞ ላይ ሰላትን ማሳጠርና ሰላትን ሰብስቦ መስገድ ይመስል ሢፈጸሙም አላህ እንደሚወድ ተናገሩ። ይህም ልክ ግዴታ ያደረጋቸው ሢሰሩ (ተግባራዊ ሲደረጉ) እንደሚወደው ነው። ምክንያቱም አላህ ባግራውም ጉዳዮች ሆነ ግዴታ ባደረገው ጉዳዮች ላይ ትእዛዙ አንድ ነውና።

فوائد الحديث

ጥራት የተገባው አላህ የደነገጋቸው ማግራሪያዎች ሲሰሩ መውደዱ አላህ በባሮቹ ላይ ያለውን እዝነት እንረዳለን።

የዚህን ሸሪዐ ምሉእነትና በሙስሊም ላይ ችግርን ያነሳ መሆኑን እንረዳለን።

التصنيفات

ሸሪዓዊ ፍርድ, Religious Assignment and its Conditions, ሸሪዓዊ አላማዎች