የአላህ መልክተኛ ሆይ! በጎ ላደርግለት እጅግ የተገባው ማን ነው?" አልኳቸው። እርሳቸውም "እናትህ ከዚያም እናትህ ከዚያም እናትህ ከዚያም አባትህ ከዚያም ቅርብ የሆኑ ዘመዶችህ" አሉ።

የአላህ መልክተኛ ሆይ! በጎ ላደርግለት እጅግ የተገባው ማን ነው?" አልኳቸው። እርሳቸውም "እናትህ ከዚያም እናትህ ከዚያም እናትህ ከዚያም አባትህ ከዚያም ቅርብ የሆኑ ዘመዶችህ" አሉ።

ከበህዝ ቢን ሐኪም ከአባቱ እንደተላለፈው: አባቱም ከአያቱ እንዳስተላለፈው እንዲህ አለ: «"የአላህ መልክተኛ ሆይ! በጎ ላደርግለት እጅግ የተገባው ማን ነው?" አልኳቸው። እርሳቸውም "እናትህ ከዚያም እናትህ ከዚያም እናትህ ከዚያም አባትህ ከዚያም ቅርብ የሆኑ ዘመዶችህ" አሉ።»

[ሐሰን ነው።] [አቡዳውድ፣ ቲርሚዚና አሕመድ ዘግበውታል።]

الشرح

ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ከሰዎች ሁሉ አስበልጠን በጎ ሊዋልለት፣ መልካም ሊሰራለት የሚገባው፣ ባማረ መልኩ ልንኗኗረው፣ ልንወዳጀውና ትስስራችንን ልናጠናክርለት የሚገባው በላጩ ሰው ማን እንደሆነ ገለፁ። እርሷም እናት ናት። ከሌሎች አካላቶች ሐቅ የእናት ሐቅ የበለጠ እንደሆነ ለማስገንዘብም ሶስት ጊዜ በመደጋገም አጽንዖት ሰጡት። ይህም የርሷ ደረጃ ከተቀሩት ሰዎች ባጠቃላይ እንደሚበልጥ ለመግለፅ ነው። ቀጥለውም ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ከእናት በመቀጠል በጎ ሊዋልለት የሚገባውን እንዲህ በማለት ገለፁ: ቀጥሎ አባት ቀጥሎ ቅርብ የሆኑ ዘመዶች አሉ። እጅግ ቅርብ በሆነ ቁጥር ሩቅ ከሆነው ዘመድ የበለጠ ዝምድናው ሊቀጠል ይገባል።

فوائد الحديث

ሐዲሡ እናትን ማስቀደም እንደሚገባ ቀጥሎ አባትን ቀጥሎ ቅርብ ዘመዶችን እንደየቅርበታቸው ደረጃ ማስቀደም እንደሚገባ ያስረዳናል።

የወላጆች ደረጃ በተለይ የእናት ደረጃ መገለፁን ተረድተናል።

ሐዲሡ ውስጥ ለእናት በጎ መስራትን ሶስት ጊዜ ደጋገሙት። ይህም ለልጆቿ ያላት ችሮታ ከሌላው የሚበልጥ ስለሆነ፤ የእርግዝናን ቀጥሎ የመውለድን ቀጥሎ የማጥባትን ጭንቅ፣ ድካምና መከራ በማየት የምታሳልፍበት ጊዜ ስለሚበዛና በዚህም የምትሰቃየው ብቻዋን ስለሆነች ነው። ከዚያም ደግሞ የማነፁን ጉዳይ ከአባት ጋር ትጋራለች።

التصنيفات

ለወላጆች መልካም የመዋል ትሩፋቶች