አጋርያንን በገንዘባችሁ፣ በነፍሳችሁና በምላሳችሁ ታገሉ።

አጋርያንን በገንዘባችሁ፣ በነፍሳችሁና በምላሳችሁ ታገሉ።

ከአነስ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል: "አጋርያንን በገንዘባችሁ፣ በነፍሳችሁና በምላሳችሁ ታገሉ።"

[ሶሒሕ ነው።]

الشرح

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና የአላህ ንግግር የበላይ እንድትሆን በተቻለ መጠን በሁሉም መንገድ ከሃዲያንን ለመታገልና እነርሱን ለመጋፈጥ በአቅም ልክ መታገልን አዘዙ። ከነዚህም መታገያዎች መካከል: የመጀመሪያው: እነርሱን በመታገል ገንዘብ ማውጣት ነው። ይህም መሳሪያ በመግዛት፣ ለሙጃሂዶች ወጪ በማድረግና በመሳሰሉት ነው። ሁለተኛው: ከሃዲያንን ለመፋለምና ለመከላከል በአካልና በነፍስ መውጣት ነው። ሶስተኛው: ወደዚህ ሃይማኖት በምላስ በመጥራት፣ በነርሱ ላይ ማስረጃ በማቆም፣ ከነርሱ በማስጠንቀቅና በነርሱ ላይ በመመለስ ነው።

فوائد الحديث

አጋርያንን በነፍስ፣ በገንዘብና በምላስ መታገል ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን። ሁሉም በአቅሙ ልክ ነው። ጂሃድ በአካል በመዋጋት ላይ ብቻ የተገደበ አይደለምና።

በጂሃድ የመጣው ትእዛዝ ግዴታን ነው የሚጠቁመው። አንዳንዴ በነፍስ ወከፍ ደረጃ ግዴታ ሲሆን አንዳንዴ ደግሞ በተወሰነ አካል ላይ ብቻ ግዴታ ይሆናል።

አላህ ጂሃድን ለብዙ ጉዳዮች ደንግጓል: ከነርሱም መካከል: የመጀመሪያ: ሺርክንና አጋርያንን መቃወም። አላህ መቼም ሺርክን አይቀበልምና። ሁለተኛ: ወደ አላህ በሚደረግ ደዕዋ መንገድ የሚጋረጡ ሳንካዎችን ማስወገጃ ነው። ሶስተኛ: የእስልምናን እምነት ከሚፃረሩት ሁሉ ነገሮች መጠበቂያ ነው። አራተኛ: ከሙስሊሞች፣ ከሀገራቸው፣ ከክብራቸውና ከገንዘባቸው መከላከያ ነው።

التصنيفات

የጂሃድ ብይን