ሐሰንና ሑሰይን የጀነት ነዋሪ ወጣቶች አለቆች ናቸው።

ሐሰንና ሑሰይን የጀነት ነዋሪ ወጣቶች አለቆች ናቸው።

ከአቡ ሰዒድ አልኹድሪይ (ረዲየላሁ ዐንሁ) -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ፦ «የአላህ መልክተኛ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል፦ "ሐሰንና ሑሰይን የጀነት ነዋሪ ወጣቶች አለቆች ናቸው።"»

[ሶሒሕ ነው።] [ቲርሚዚና አሕመድ ዘግበውታል።]

الشرح

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና የርሳቸው ልጅ ልጆች የሆኑትና የዐሊይ ቢን አቢ ጧሊብና የፋጢማ ቢንት ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ልጆች የሆኑት ሐሰንና ሑሰይን ወጣት ሆኖ ሞቶ በአላህ ችሮታ ጀነት ለገባ ሰው ሁሉ አለቃ እንደሆኑ ወይም ከነቢያትና ከነቢዩ ቅን ምትክ መሪዎች ውጪ ላሉ የጀነት ወጣት ነዋሪዎች በሙሉ አለቃ እንደሆኑ ተናገሩ።

فوائد الحديث

ይህ ሐዲሥ የሐሰንና የሑሰይንን (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ግልፅ የሆነ ደረጃ ያስረዳናል።

በሐዲሡ ሀሳብ ዙሪያ ከተባሉት መካከል: ይህ ሐዲስ በተወራበት ወቅት በዛ ዘመን የጀነት ነዋሪ ለሆኑ ወጣቶች አለቆች ናቸው፤ ወይም እንደነቢያቶችና ኹለፋዎቹ አጠቃላይ የሆነ በላጭነት ያልመጣባቸው ከሆኑ ወጣቶች ሁሉ በላጭ ናቸው፤ ወይም እነርሱ ክብርን መጠበቅ፣ ቸርነትና ጀግንነትን የመሰሉ በወጣትነት ባህሪ ለተላበሱ ሰዎች አለቃ ናቸው። በዚህም የወጣትነት እድሜ አልመጣምና። ሐሰንና ሑሰይንም ጎልምሰው ነው የሞቱትና።

التصنيفات

የነቢዩ ቤተሰቦች ደረጃ