ከናንተ በፊት የነበሩትን (ሕዝቦች) ጎዳና ስንዝር በስንዝር፣ ክንድ በክንድ ትከተላላችሁ።

ከናንተ በፊት የነበሩትን (ሕዝቦች) ጎዳና ስንዝር በስንዝር፣ ክንድ በክንድ ትከተላላችሁ።

ከአቡ ሰዒድ አልኹድሪይ (ረዲየላሁ ዐንሁ) -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንዲህ አሉ፦ «የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል፦ "ከናንተ በፊት የነበሩትን (ሕዝቦች) ጎዳና ስንዝር በስንዝር፣ ክንድ በክንድ ትከተላላችሁ። የወከሎ ቤት (ጉድጓድ) ቢገቡ እንኳ ትከተሏችኋላችሁ።" እኛም "የአላህ መልክተኛ ሆይ! ክርስቲያኖችንና አይሁዶችን ነውን?" አልናቸው። እርሳቸውም "ታዲያ ሌላ ማን ነው?" አሉን።»

[ሶሒሕ ነው።] [Al-Bukhari and Muslim with its two versions]

الشرح

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከርሳቸው ዘመን በኋላ የአንዳንድ ኡመታቸው ሁኔታ እንዴት እንደሚሆን ተናገሩ። እርሱም የአይሁዶችንና የክርስቲያኖችን መንገድ በእምነታቸው፣ በድርጊታቸው፣ በልማዳቸውና ባህላቸው እጅግ በረቀቀ መንገድ ስንዝር በስንዝር፣ ክንድ በክንድ መከተል ነው። የወከሎ ቤት ቢገቡ እንኳ እነሱም ከኋላቸው ተከትለዋቸው ይገባሉ።

فوائد الحديث

ይህንን ከመከሰቱ በፊት መናገራቸውና እንደተናገሩት መከሰቱ ከነቢይነታቸው ምልክቶች መካከል አንዱ ምልክት ነው።

ሙስሊሞች ከከሀዲያን ጋር በእምነታቸው ወይም በአምልኳቸው ወይም በበዓላቸው ወይም የነሱ ብቻ መለዮ በሆኑ ነገሮች ከመመሳሰል መከልከላቸውን እንረዳለን።

ሀሳባዊ የሆኑ ነገሮችን ህዋሳዊ በሆኑ ነገሮች መስሎ ማብራራት ከኢስላማዊ የማስተማር ዘዴዎች መካከል አንዱ እንደሆነ እንረዳለን።

ወከሎ ማለት:- መኖርያው እጅግ ጨለማና ሽታው የሚገማ ጉሬ ውስጥ ሲሆን በረሃ ላይ የሚበዛ ተሳቢ እንስሳ ነው። ምሳሌው በልዩ ሁኔታ በወከሎ ቤት የተደረገው ጉሬው እጅግ ጠባብና ዝቃጭ ለማሳየት ነው። ከመሆኑም ጋር ግን የነርሱን ፈለግ በማፈንፈንና መንገዳቸውን በመከተል በኩል ካላቸው ተነሳሽነት አንፃር በዚህ መሰል ጠባብና ዝቃጭ ቦታ ቢገቡ እንኳ ይከተሏቸዋል። አላህ ይጠብቀን!

التصنيفات

የተከለከለው መመሳሰል