(ግዴታነቱን) አምኖ እና ምንዳውን ከአላህ አስቦ የረመዳንን ወር የፆመ ሰው ያለፈ ወንጀሉ ይማርለታል።

(ግዴታነቱን) አምኖ እና ምንዳውን ከአላህ አስቦ የረመዳንን ወር የፆመ ሰው ያለፈ ወንጀሉ ይማርለታል።

ከአቡ ሁረይራ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል፦ የአላህ መልዕክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል፦ "(ግዴታነቱን) አምኖ እና ምንዳውን ከአላህ አስቦ የረመዳንን ወር የፆመ ሰው ያለፈ ወንጀሉ ይማርለታል።"

[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]

الشرح

ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና የረመዳንን ወር በአላህ አምኖ፣ በፆም ግዴታነትና አላህ ለፆመኞች ያዘጋጀውን የደለበ ምንዳና አጅር እውነት ብሎ እንዲሁም ፆሙም ለይዩልኝና ይስሙልኝ ሳይሆን የአላህን ፊት ፈልጎበት የፆመ ሰው ያለፈው ወንጀሉን እንደሚማር ነገሩን።

فوائد الحديث

በረመዳን ፆምም ይሁን በሌሎች መልካም ስራዎች ላይ ኢኽላስ ያለውን ትሩፋትና አንገብጋቢነትን እንረዳለን።

التصنيفات

የጾም ትሩፋት