ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሌሊት የተነሱ ጊዜ አፋቸውን በመፋቂያ ይፍቁ ነበር።

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሌሊት የተነሱ ጊዜ አፋቸውን በመፋቂያ ይፍቁ ነበር።

ከሑዘይፋ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሌሊት የተነሱ ጊዜ አፋቸውን በመፋቂያ ይፍቁ ነበር።

[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]

الشرح

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) አብዝተው የሚፍቁና በመፋቅም ላይ የሚያዙ ነበሩ። አንዳንድ ወቅቶች ላይም አጠንክረው ሱናውን ይተገብሩ ነበር። ከነዛም ወቅቶች መካከል: ሌሊት በሚቆሙበት ወቅት መፋቅ ነው። ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) አፋቸውን በመፋቂያ ይፍቁና ያፀዱ ነበር።

فوائد الحديث

ከሌሊት እንቅልፍ በኋላ የመፋቅ ድንጋጌ አፅንዖት የተሰጠው መሆኑን እንረዳለን። ይህም እንቅልፍ የአፍ ጠረን እንዲለወጥ አንዱ ምክንያት ስለሆነ ነው። መፋቂያም የማፅጃ አንዱ መሳሪያ ነው።

የአፍ ጠረን ወደ መጥፎ ጠረን በሚለወጥበት ወቅት ባጠቃላይ መፋቅ አፅንዖት ተሰጥቶት የተደነገገ ጉዳይ መሆኑን እንረዳለን። ይህም ቀደም ተብሎ የተጠቀሰውን ሀሳብ በመያዝ ነው።

ጥቅል በሆነ መልኩ ማፅዳት የተደነገገ ጉዳይ መሆኑን እንረዳለን። ንፅህና ከነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሱናና ከምርጥ ስነ ምግባር አንዱ ነው።

አፍን ባጠቃላይ መፋቅ ሲባል ጥርሶችን፣ ድድንና ምላስንም ያካትታል።

መፋቂያ ማለት "አራክ" ከሚባል ዛፍ ወይም ከሌላ የዛፍ አይነት የሚቆረጥ እንጨት ነው። አፍንና ጥርስን ለማፅዳትም ያገለግላል። አፍን ያፀዳል፣ መጥፎ ጠረንንም ያስወግዳል።

التصنيفات

ተፈጥሯዊ ሱናዎች, ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በመፀዳዳት ወቅት የነበራቸው መመሪያ