إعدادات العرض
ምግብ ቀርቦ አልያም ሁለቱ ቆሻሻዎች እያጨናነቁት ሶላት የለም።
ምግብ ቀርቦ አልያም ሁለቱ ቆሻሻዎች እያጨናነቁት ሶላት የለም።
ከእናትችን ዓኢሻ (ረዲየሏሁ ዐንሃ) - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና እንደተላለፈው እንዲህ ብላለች፦ "የአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ፦ "ምግብ ቀርቦ አልያም ሁለቱ ቆሻሻዎች እያጨናነቁት ሶላት የለም።"
[ሶሒሕ ነው።] [ሙስሊም ዘግበውታል።]
الترجمة
عربي বাংলা Bosanski English Español فارسی Français Bahasa Indonesia Русский Tagalog Türkçe اردو 中文 हिन्दी Tiếng Việt සිංහල ئۇيغۇرچە Kurdî Hausa Português മലയാളം မြန်မာ Deutsch 日本語 پښتو অসমীয়া Shqip Svenska cs ગુજરાતી Yorùbá Nederlands తెలుగు Kiswahili தமிழ் ไทย دری Кыргызча Lietuvių rw so नेपालीالشرح
የአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የሰጋጅ ነፍስ የሚጓጓውና ልቡ የተንጠለጠለበት ምግብ ቀርቦ መስገድን ከለከሉ። ልክ እንደዚሁ በቆሻሻው ግፊት ስለሚጠመድም ሁለቱ ቆሻሾች እያጨናነቁት (እነርሱም ሽንትና አይነ ምድር ናቸው።) ከመስገድ ከለከሉ።فوائد الحديث
አንድ ሰጋጅ ወደ ሶላት ከመግባቱ በፊት ከሶላቱ የሚያዘናጋውን ነገር ባጠቃላይ ማራቅ ይገባዋል።