አይሁዶች ቁጣ የሰፈነባቸው ሲሆኑ ክርስቲያኖች ደግሞ የተሳሳቱ ናቸው።

አይሁዶች ቁጣ የሰፈነባቸው ሲሆኑ ክርስቲያኖች ደግሞ የተሳሳቱ ናቸው።

ከዓዲይ ቢን ሓቲም እንደተላለፈው: "ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ አሉ፦ "አይሁዶች ቁጣ የሰፈነባቸው ሲሆኑ ክርስቲያኖች ደግሞ የተሳሳቱ ናቸው።"

[ሶሒሕ ነው።] [ቲርሚዚ ዘግበውታል።]

الشرح

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) አይሁዶች እውነትን እያወቁ ባለመተግበራቸው አላህ የተቆጣባቸው ህዝቦች እንደሆኑ ተናገሩ። ክርስቲያኖች ደግሞ ያለ ዕውቀት የሚሰሩ ስለሆኑ የተሳሳቱ ህዝቦች ናቸው።

فوائد الحديث

ዕውቀትና ተግባርን ሰብስቦ መሄድ ቁጣ ከሰፈነባቸውም ከተሳሳቱትም ሰዎች መንገድ መዳኛ መሆኑን እንረዳለን።

ከአይሁዶችና ክርስቲያኖች መንገድ መጠንቀቅና ቀጥተኛ የሆነውን የኢስላምን ጎዳና አጥብቀን መያዝ እንዳለብን እንረዳለን።

በመሰረቱ አይሁዶችም ክርስቲያኖችም የተሳሳቱና ቁጣ የሰፈነባቸው ህዝቦች ናቸው። ነገር ግን ልዩ መገለጫቸው የአይሁዶቹ ቁጣ የሰፈነባቸው መሆናቸው ሲሆን የክርስቲያኖች ልዩ መገለጫ ደግሞ መሳሳታቸው ነው።

التصنيفات

ኢስላም, የአንቀፆች ተፍሲር (ማብራሪያ)