አላህ ሆይ! እኔ ከቀብር ቅጣት፣ ከእሳት ቅጣት፣ ከህይወትና ሞት ፈተና እና ከመሲሕ ደጃል ፈተና ባንተው እጠበቃለሁ።' እያሉ ዱዓእ ያደርጉ ነበር።

አላህ ሆይ! እኔ ከቀብር ቅጣት፣ ከእሳት ቅጣት፣ ከህይወትና ሞት ፈተና እና ከመሲሕ ደጃል ፈተና ባንተው እጠበቃለሁ።' እያሉ ዱዓእ ያደርጉ ነበር።

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል፦ "የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና): 'አሏሁመ ኢኒ አዑዙ ቢከ ሚን ዓዛቢል ቀብሪ ወሚን ዓዛቢ‐ን‐ናር ወሚን ፊትነቲል መሕያ ወል መማት ወሚን ፊትነቲል መሲሒ‐ድ‐ደጃል' 'ትርጉሙም: አላህ ሆይ! እኔ ከቀብር ቅጣት፣ ከእሳት ቅጣት፣ ከህይወትና ሞት ፈተና እና ከመሲሕ ደጃል ፈተና ባንተው እጠበቃለሁ።' እያሉ ዱዓእ ያደርጉ ነበር።" በሙስሊም ዘገባ 'አንዳችሁ ከመጨረሻው ተሸሁድ ያጠናቀቀ ጊዜ ከአራት ነገሮች በአላህ ይጠበቅ: ከጀሀነም ቅጣት፣ ከቀብር ቅጣት፣ ከህይወትና ሞት ፈተናና ከመሲሕ ደጃል ክፋት።'"

[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]

الشرح

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከመጨረሻው ተሸሁድ በኋላ ከሶላት ከማሰላመታቸው በፊት ከአራት ነገሮች በአላህ ይጠበቁ ነበር። እኛንም በአላህ ከነርሱ እንድንጠበቅ አዘዙን። የመጀመሪያው: ከቀብር ቅጣት ነው። ሁለተኛው: የትንሳኤ ቀን ከእሳት ቅጣት ነው። ሶስተኛው: ከህይወት ፈተናዎች ሲባል ክልክል ከሆኑ ዓለማዊ ዝንባሌዎችና አጥማሚ ማደናገሪያዎች፤ እንዲሁም በሞት ሰአት ከሚያጋጥሙ ፈተናዎች ሲባል ደግሞ በጣእረ ሞት ሰአት ከኢስላም ወይም ሱና መጥመምን የመሰሉ ወይም በሁለቱ መላእክት መጠየቅን ከመሰለ የቀብር ፈተና ማለት ነው። አራተኛ: በመጨረሻ ዘመን የሚወጣ ከሆነው ከመሲሕ ደጃል ፈተና ነው። አላህ በርሱ አማካኝነት ባሮቹን ይፈትናል። ዱዓው ላይ እርሱ ተለይቶ የተጠቀሰው የርሱ ፈተናና ማጥመሙ ከባድ ስለሆነ ነው።

فوائد الحديث

እነዚህ መጠበቂያ ዱዓዎች ከዱንያና ከመጨረሻው ዓለም ክፋቶች መጠበቅን ከሰበሰቡ አንገብጋቢና ጠቅላይ ከሆኑ ዱዓዎች መካከል ናቸው።

የቀብር ቅጣት የተረጋገጠና እውነት መሆኑን እንረዳለን።

የፈተናን አደገኝነት እና ከፈተና ለመዳን በአላህ መታገዝና ዱዓ ማድረግ እንደሚገባ እንረዳለን።

የደጃል መውጣት የተረጋገጠ መሆኑንና ፈተናው ከባድ መሆኑን እንረዳለን።

ከመጨረሻው ተሸሁድ በኋላ ይህን ዱዓ ማለት እንደሚወደድ እንረዳለን።

ከመልካም ስራ በኋላ ዱዓ ማድረግ እንደሚወደድ እንረዳለን።

التصنيفات

የሶላት አዝካሮች