ሰውዬው አማኝ ሆኖ ያነጋና ከሀዲ ሆኖ የሚያመሽበት፤ ወይም አማኝ ሆኖ ያመሽና ከሀዲ ሆኖ የሚያነጋበት፤ እምነቱንም በአለማዊ ሸቀጥ እስከመሸጥ የሚያደርሱ የድቅድቅ ጨለማ ቁራጭ የመሰሉ…

ሰውዬው አማኝ ሆኖ ያነጋና ከሀዲ ሆኖ የሚያመሽበት፤ ወይም አማኝ ሆኖ ያመሽና ከሀዲ ሆኖ የሚያነጋበት፤ እምነቱንም በአለማዊ ሸቀጥ እስከመሸጥ የሚያደርሱ የድቅድቅ ጨለማ ቁራጭ የመሰሉ ፈተናዎች ከመምጣታቸው በፊት በመልካም ስራ ተቻኮሉ።

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል: "ሰውዬው አማኝ ሆኖ ያነጋና ከሀዲ ሆኖ የሚያመሽበት፤ ወይም አማኝ ሆኖ ያመሽና ከሀዲ ሆኖ የሚያነጋበት፤ እምነቱንም በአለማዊ ሸቀጥ እስከመሸጥ የሚያደርሱ የድቅድቅ ጨለማ ቁራጭ የመሰሉ ፈተናዎች ከመምጣታቸው በፊት በመልካም ስራ ተቻኮሉ።"

[ሶሒሕ ነው።] [ሙስሊም ዘግበውታል።]

الشرح

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) መልካም ስራ ከመፈፀም የሚከለክሉና የሚያቅቡ ፈተናና ማምታቻዎች መጥተው መልካም ስራ መስራት ከባድ ከመሆኑ በፊት አማኞች ወደ መልካም ስራ እንዲቻኮሉና እንዲያበዙ አነሳሱ። ይህም ፈተና እንደ ሌሊት ቁራጭ ድቅድቅ ጨለማ በመሆኑ እውነቱ ከሀሰት ጋር ተደበላልቆ ለሰዎች እውነትን ከውሸት መለየት የሚከብድበት ፈተና ነው። ከፈተናዋ መክበድ የተነሳ ሰውዬው አማኝ ሆኖ አንግቶ ከሀዲ ሆኖ እስኪያመሽ፤ አማኝ ሆኖ አምሽቶ ከሀዲ ሆኖ እስኪያነጋና ጠፊ በሆነው አለማዊ ጥቅም ሃይማኖቱን እስኪተው ድረስ ሰዎች ይዋልላሉ።

فوائد الحديث

ሃይማኖቱን በአግባቡ ከመተግበር የሚከለክሉ ግርዶሾች ከመምጣታቸው በፊት ሃይማኖትን አጥብቆ መያዝና ወደ መልካም ስራ መቻኮል ግዴታ መሆኑን እንረዳለን።

በመጨረሻው ዘመን አጥማሚ ፈተናዎች ተከታትለው እንደሚመጡ መጠቆማቸው። ይህም አንድ ፈተና በተወገደች ቁጥር ሌላ ፈተና ይከተላታል።

የሰው ልጅ እምነት በደከመ ጊዜና ለገንዘብም ሆነ ለሌላ ዓለማዊ ጉዳዮች እምነቱን አሳልፎ ከሰጠ ይህ ከእምነቱ ለመጣመም፣ እምነቱን ለመተዉና ከፈተና ጋር አብሮ ለመነዳቱ ሰበብ ይሆንበታል።

እዚህ ሐዲሥ ውስጥ መልካም ስራዎች ከፈተና ለመዳን ምክንያት እንደሆኑ ይጠቁማል።

ፈተናዎች በሁለት ይከፈላሉ:- አንዱ የማምታቻ (የሹበሃ) ፈተናዎች ሲሆን መፍትሄውም ዕውቀት ነው። ሌላው ደግሞ የዝንባሌ/ ፍላጎት (የሸህዋ) ፈተናዎች ሲሆን መፍትሄውም ኢማንና ትእግስት ነው።

ይህ ሐዲሥ ስራው ያነሰ ሰው ፈተና ወደርሱ በፍጥነት እንደሚመጣና ስራው የበዛ ሰው ደግሞ በሰራው ስራ (ተመፃድቆ) መሸወድ እንደማይገባውና ይልቁንም ጨምሮ ማብዛት እንዳለበት ይጠቁማል።

التصنيفات

የኢማን ቅርንጫፍ