አስር ጊዜ 'ላ ኢላሃ ኢለሏህ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለህ ፤ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁወ ዓላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር' ያለ ሰው

አስር ጊዜ 'ላ ኢላሃ ኢለሏህ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለህ ፤ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁወ ዓላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር' ያለ ሰው

ከአቡ አዩብ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፦ "አስር ጊዜ 'ላ ኢላሃ ኢለሏህ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለህ ፤ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁወ ዓላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር' ያለ ሰው ከኢስማዒል ዘሮች የሆኑ አራት ነፍሶችን ነፃ እንዳወጣ ይቆጠርለታል።"

[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]

الشرح

በዚህ ሐዲሥ ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንደሚነግሩን ይህንን ውዳሴ ያለ፦ "ላ ኢላሃ ኢለሏህ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለህ ፤ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁወ ዓላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር" ትርጉሙም: ከአላህ ውጪ በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም፤ ብቸኛና ለሱ አጋር የለውም፤ ጥራት የተገባው አላህ በምሉዕ ንግስና የተለየ ነው፤ ከሱ ውጪ ያሉት የማይገባቸውን ውዳሴና ሙገሳ ከውዴታና ልቅና ጋር በብቸኝነት የተገባው ነው ፤ እርሱም አንዳችም የማያቅተው ቻይ ነው። ይህንን ታላቅ ውዳሴም በቀን አስር ጊዜ የደጋገመም ሰው በነርሱ ላይ የአላህ ሶላትና ሰላም ይስፈንና የኢብራሂም ልጅ ከሆኑት ከኢስማዒል ዘሮች አራት ባሮችን ከባርነት ነፃ እንዳወጣ ሰው ምንዳ አምሳያ ለርሱ ይኖረዋል። የኢስማዒል ዐለይሂ ሰላም ዘሮች የተለዩትም እነርሱ ከሌሎች የላቁ ስለሆኑ ነው።

فوائد الحديث

የዚህ ውዳሴ ትሩፋት አላህን በተመላኪነት፣ በንግስና፣ በምስጋናና በተሟላ ችሎታ መነጠልን ያካተተ ነው።

ይህንን ውዳሴ አከታትሎም ሆነ በተለያየ ቆይታ ያለ ሰው የዚህን ውዳሴ ምንዳ እንደሚያገኝ እንረዳለን።

التصنيفات

የዚክር ትሩፋቶች