የነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ስነምግባር ቁርአን ነበር።' አለችኝ።

የነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ስነምግባር ቁርአን ነበር።' አለችኝ።

ሰዕድ ቢን ሂሻም ቢን ዓሚር እናታችን ዓኢሻህ ዘንድ -አላህ መልካም ስራዋን ይውደድላትና- የገባ ወቅት እንዲህ አለ: "የሙእሚኖች እናት ሆይ! ስለአላህ መልክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ስነምግባር ንገሪኝ! እሷም 'ቁርአን አትቀራምን?' አለችኝ። እኔም 'እንዴታ!' አልኩኝ። እሷም ' የነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ስነምግባር ቁርአን ነበር።' አለችኝ።"

[ሶሒሕ ነው።] [ሙስሊም ዘግበውታል።]

الشرح

የአማኞች እናት የሆነችው ዓኢሻህ -አላህ መልካም ስራዋን ይውደድላትና- ስለነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ስነምግባር ተጠየቀች። ጠያቂውን ሁሉንም ምሉዕ ባህሪያት ወደ ሰበሰበው ወደ ተከበረው ቁርአን በመመለስ ጠቅላይ በሆነ ንግግር መለሰችለት። ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ቁርአናዊውን ስነምግባር የተላበሱ ፤ ቁርአን ያዘዘውን ይፈፅሙ፣ ቁርአን የከለከለውን ደግሞ ይርቁ እንደነበር፤ የሳቸው ስነምግባር በቁርአን መስራት ፣ ድንበሩ ላይ መቆም፣ የቁርአንን አዳብ መላበስ ፣ ምሳሌዎቹንና ታሪኮቹን ማስተንተን ነበር ብላ መለሰችለት።

فوائد الحديث

ቁርአናዊ ስነምግባር በመላበሳቸው ነቢዩን ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም አርአያ ማድረግ ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።

የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ስነምግባር መሞገሱ። የሳቸው ስነምግባር ከወሕይ ምንጭ የተቀዳ ነውና።

ቁርአን ለሁሉም የተከበሩ ስነምግባሮች ምንጭ መሆኑን እንረዳለን።

ስነምግባር በኢስላም ሁሉንም የሃይማኖቱን ክፍሎች ያጠቃልላል፤ ይህም ትእዛዛትን በመፈፀምና ክልከላውን በመራቅ ነው።

التصنيفات

ስነ-ምግባሪያዊ ባህሪያቸው, ስነ-ምግባሪያዊ ባህሪያቸው