የአላህን መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ እንደሌለ ሙሐመድም የአላህ መልክተኛ መሆናቸውን በመመስከር፣ ሶላትን በማቋቋም፣…

የአላህን መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ እንደሌለ ሙሐመድም የአላህ መልክተኛ መሆናቸውን በመመስከር፣ ሶላትን በማቋቋም፣ ዘካን በመስጠት፣ መሪዎችን በመስማትና በመታዘዝ ላይ፣ ለሁሉም ሙስሊም ተቆርቋሪ (ታማኝ/ ቅን) በመሆን ላይ ቃል ኪዳን ተጋቧሃቸው።

ከጀሪር ቢን ዐብደላህ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል፦ "የአላህን መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ እንደሌለ ሙሐመድም የአላህ መልክተኛ መሆናቸውን በመመስከር፣ ሶላትን በማቋቋም፣ ዘካን በመስጠት፣ መሪዎችን በመስማትና በመታዘዝ ላይ፣ ለሁሉም ሙስሊም ተቆርቋሪ (ታማኝ/ ቅን) በመሆን ላይ ቃል ኪዳን ተጋቧሃቸው።"

[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]

الشرح

ሶሐቢዩ ጀሪር ቢን ዐብደላህ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ዘንድ እንደነበርና እርሳቸውንም ቃልኪዳን እንደተጋባ ተናገረ። ቃል የተጋባውም በተውሒድ (አላህን በብቸኝነት በማምለክ)፣ በቀንና ምሽት አምስት ግዴታ የሆኑትን ሶላቶች ‐ መስፈርቶቿን፣ ማእዘናቶቿን፣ ግዴታዎቿንና ሱናዎቿን በማሟላት ‐ በመስገድ፣ ግዴታ የሆነውን ዘካ በመስጠት ላይ ‐ ዘካ: ግዴታ የሆነ ገንዘባዊ አምልኮ ሲሆን ከሀብታሞች ተወስዶ ለሚገባቸው ድሆችና ለሌሎችም የሚሰጥ ነው፣ ‐ መሪዎችን በመታዘዝ ላይ፣ ለሁሉም ሙስሊም ተቆርቋሪ (ቅን) በመሆን ላይ ‐ ይህም: ለሙስሊም ጥቅም በመጓጓት፣ መልካምን ለርሱ በማድረስ፣ በንግግርም ሆነ በተግባር መጥፎን ነገር ከርሱ በመከላከል ነው።

فوائد الحديث

የሶላትና የዘካን አንገብጋቢነት እንረዳለን። እነርሱም የኢስላም ማእዘናት ናቸው።

የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከሶሐቦች (ረዲየሏሁ ዐንሁም) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና ጋር በዚህ ጉዳይ ቃል ኪዳን መጋባታቸው በሙስሊሞች መካከል የታማኝነትና የመመካከርን አንገብጋቢነት ያስረዳል።

التصنيفات

የሶላት ትሩፋት