ስራዎች የሚለኩት በኒያዎች (በሀሳብ) ብቻ ነው። ሁሉም ሰው የሚያገኘው ያሰበውን ነው።

ስራዎች የሚለኩት በኒያዎች (በሀሳብ) ብቻ ነው። ሁሉም ሰው የሚያገኘው ያሰበውን ነው።

ከዑመር ቢን አልኸጧብ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: የአላህ መልክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፦ "ስራዎች የሚለኩት በኒያ (በሀሳብ) ብቻ ነው። ሰውየው የሚያገኘው ያሰበውን ነው። ስደቱ ወደ አላህና መልክተኛው የሆነ ሰው የስደቱ (ምንዳም) ወደ አላህና መልክተኛው ነው። ስደቱ ለዱንያ ጥቅማጥቅም ለማግኘት ወይም ሴትን ለማግባት የሆነ ሰው የስደቱ (ምንዳ) ወደ ተሰደደበት ነገር ወደዛው ነው።" በቡኻሪ ዘገባ ደግሞ፦ "ስራዎች የሚለኩት በኒያዎች (በሀሳብ) ብቻ ነው። ሁሉም ሰው የሚያገኘው ያሰበውን ነው።"

[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]

الشرح

ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ሁሉም ስራዎች ግምት የሚሰጣቸው በኒያ እንደሆነ አብራሩ። ይህ ብይን በአምልኳዊም ጉዳይ ሆነ ከሰው ጋር ባሉ መስተጋብሮች ሁሉንም ስራዎች የሚያጠቃልል ነው። በስራው የሆነን ጥቅም ያሰበ ሰው ከዛች ጥቅም በስተቀር ሌላ አያገኝም። ምንዳም የለውም። በስራው ወደ አላህ መቃረብን ያሰበ ሰው ደግሞ እንደ መብላትና መጠጣት የመሰሉ ተለምዷዊ ስራ ቢሆንም እንኳ ሰርቶ በስራው ምንዳና አጅርን ያገኛል። ቀጥለውም ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ስራዎች በውጫዊ ይዘታቸው ሲታዩ ተመሳሳይ ከመሆናቸውም ጋር ኒያ በስራዎች ላይ የሚያሳድረውን ተፅእኖ ለማብራራት ምሳሌ ጠቀሱ። በስደቱና ሀገሩን በመተዉ የአላህን ውዴታ ማግኘትን ያሰበ ስደቱ ሸሪዐዊና ተቀባይነት ያለው ስደት ነው። ኒያው እውነተኛ ስለሆነም ይመነዳበታል። በስደቱ ግን እንደ ገንዘብ፣ ክብር፣ ንግድና ሚስት የመሳሰሉ ዓለማዊ ጥቅም የፈለገ ሰው ከስደቱ ይህችን ያሰባትን ጥቅም በስተቀር ሌላ አያገኝም። ከምንዳና አጅርም ምንም እጣ ፈንታ እንደሌለው ገለፁ።

فوائد الحديث

በኢኽላስ ላይ መበረታታቱ ፤ አላህ የሱ ፊት ተፈልጎበት የተሰራን ስራ ካልሆነ በስተቀር ምንም ስራ አይቀበልምና።

አንድ ሸሪዓዊ ብይኖች የሚመለከቱት ዕድሜ ክልል ላይ የደረሰ ሰው ወደ አላህ የሚቃረብበትን ስራ በተለምዷዊ እሳቤ ቢሰራው በስራው ወደ አላህ መቃረብን እስኪያስብ ድረስ በሷ አማካኝነት ምንም ምንዳ አይኖረውም።

التصنيفات

የቀልብ ተግባራት