መላዕክቶች ውሻና ስዕል ወዳለበት ቤት አይገቡም።

መላዕክቶች ውሻና ስዕል ወዳለበት ቤት አይገቡም።

ከአቡ ጦልሓ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል: "መላዕክቶች ውሻና ስዕል ወዳለበት ቤት አይገቡም።"

[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪ ዘግበውታል። - ሙስሊም ዘግበውታል። - ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]

الشرح

ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የእዝነት መላዕክቶች ውሻና ነፍስ ያላቸው የፍጡራን ስዕል ወዳለበት ቤት እንደማይገቡ ተናገሩ። ይህም ነፍስ ያለበት ምሥል አስከፊ ወንጀል ስለሆነ፤ ከአላህ አፈጣጠር ጋር መፎካከር ስለሆነ፤ የሽርክ መዳረሻም ስለሆነ፤ አንዳንዶቹ ምሥሎችም ከአላህ ውጪ የሚመለኩ ምሥሎች ስለሆኑ ነው። ውሻ ያለበት ቤት ከመግባት የመቆጠባቸው ምክንያት ደግሞ: በብዛት ነጃሳ ስለሚመገብ፤ አንዳንዶቹም ሸይጧን ተብለው ስለተጠሩ ነው። መላዕክት ደግሞ የሸይጧን ተቃራኒ ናቸው። በተጨማሪ የውሻ ሽታ አፀያፊ ስለሆነ ነው። መላዕክት ደሞ መጥፎ ሽታን ይጠላሉ። ስለዚህ ውሻን ማሳደግ ተከለከለ። የሚያሳድግ ሰውም የእዝነት መላዕክት ቤቱ ባለመግባታቸው፤ ለቤቱ ዱዓእ ባለማድረጋቸው፤ ለርሱ ምህረት ባለመጠየቃቸው፤ ለርሱና ለቤቱ በረከት ባለመጠየቃቸው፤ የሸይጧንን ጉዳት ከርሱ ላይ ባለመከላከላቸው ተቀጣ።

فوائد الحديث

የአደን ውሻ ወይም የከብት ጠባቂ የሆነ ውሻ ወይም የአዝርዕት ጠባቂ የሆነ ውሻ ካልሆነ በቀር ውሻን ማሳደግ ክልክል መሆኑን እንረዳለን።

ስዕል ማስቀመጥ መላዕክት የሚሸሹት ከሆኑ ቆሻሻ ጉዳዮች አንዱ ነው። በአንድ ስፍራ ስዕል መኖሩ እዝነትን እንድንነፈግ ምክንያት ይሆነናል። ውሻም ልክ እንደዚሁ ነው።

ውሻ ወይም ስዕል ያለበት ቤት ውስጥ የማይገቡት መላዕክቶች የእዝነት መላዕክቶች ናቸው እንጂ ስራን የሚመዘግቡና ሌሎች እንደ መልዐከ ሞት የመሰሉ የስራ ድርሻ ያላቸው መላዕክቶች ግን ሁሉም ቤት ይገባሉ።

ግድግዳና ሌሎች ነገሮች ላይ ነፍስ ያላቸውን ፍጡራን ስዕላቸውን ማንጠልጠል ክልክል መሆኑን እንረዳለን።

ኸጧቢ እንዲህ ብለዋል: «መላዕክት ውሻ ወይም ስዕል ያለበት ቤት የማይገቡት ማስቀመጡ ክልክል የሆኑ ውሻዎችንና ስዕሎችን ነው። ክልክል ያልሆኑ የአደን ውሻ፣ የአዝርዕትና ከብቶች ጠባቂ የሆኑ ውሻዎችን እንዲሁም ምንጣፍ ላይ፣ ትራስ ላይና የመሳሰሉት ግን በነርሱ ምክንያት መላዕክት ከመግባት አይቆጠቡም።

التصنيفات

አላህን በተመላኪነቱ መነጠል