إعدادات العرض
ጀነት ወደ እያንዳንዳችሁ ከጫማው ማሰሪያ የበለጠ ቅርብ ናት። እሳትም እንደዚሁ።
ጀነት ወደ እያንዳንዳችሁ ከጫማው ማሰሪያ የበለጠ ቅርብ ናት። እሳትም እንደዚሁ።
ከኢብኑ መስዑድ ረዲየሏሁ ዐንሁ እንደተላለፈው እንዲህ ብሏል፡ "የአሏህ መልዕክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል፡ "ጀነት ወደ እያንዳንዳችሁ ከጫማው ማሰሪያ የበለጠ ቅርብ ናት። እሳትም እንደዚሁ።"
[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪ ዘግበውታል።]
الترجمة
العربية বাংলা Bosanski English Español فارسی Français Bahasa Indonesia Türkçe اردو 中文 हिन्दी Tagalog Kurdî Hausa Português മലയാളം తెలుగు Kiswahili தமிழ் සිංහල မြန်မာ Русский Deutsch 日本語 پښتو Tiếng Việt অসমীয়া Shqip Svenska Čeština ગુજરાતી Yorùbá Nederlands ئۇيغۇرچە ไทย دری Български Fulfulde Magyar ಕನ್ನಡ Кыргызча Lietuvių Malagasy or Română Kinyarwanda тоҷикӣ O‘zbek Akan नेपाली Moore Azərbaycan Wolof Oromoo Soomaali Українська bm km rn ქართული Македонски Српски Ελληνικάالشرح
ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ለሰው ልጅ ጀነትም ይሁን ጀሀነም በእግሩ ላይ እንዳለው የጫማው ማሰሪያ ቅርብ መሆናቸውን ተናገሩ። ምክንያቱም (ሳያስበው) አሏህን የሚያስደስት የሆነን መልካም ስራ ይሰራና በዛ ሰበብ ጀነት ይገባል። ወይም መጥፎ ስራ ይሰራና ጀሀነም ለመግባት ሰበብ ይሆንበታል።فوائد الحديث
ትንሽ ቢሆንም መልካም ስራ ላይ መበርታትና ትንሽ ቢሆንም ከክፋት መጠንቀቅ እንደሚገባ እንረዳለን።
ሙስሊም በህይወቱ በራሱ ሁኔታ ሳይሸወድ ሁሌም በተስፋና በስጋት መካከል ሊሆን እና እውነት ላይ እንዲያፀናውም ጥራት የተገባው አሏህን ሊማፀን የግድ እንደሚገባው እንረዳለን።
التصنيفات
የጀነትና እሳት ባህሪዎች