ዕውቀትን ዑለሞችን ልትፎካከሩበት (በሊቃውንት ፊት ለመታየት)፣ ቂሎችን ልትሟገቱበት

ዕውቀትን ዑለሞችን ልትፎካከሩበት (በሊቃውንት ፊት ለመታየት)፣ ቂሎችን ልትሟገቱበት

ከጃቢር ቢን ዐብደላህ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦ "ዕውቀትን ዑለሞችን ልትፎካከሩበት (በሊቃውንት ፊት ለመታየት)፣ ቂሎችን ልትሟገቱበት፣ በመድረኮች ላይ ቅድሚያ እንድትመረጡበት በማለም እንዳትቀስሙ። ይህን የፈፀመ (ለርሱ) እሳት አለው እሳት አለው።"

[ሶሒሕ ነው።] [ኢብኑ ማጀህ ዘግበውታል።]

الشرح

ዑለሞችን ለመወዳደርና ለመፎካከር፣ እኔ እንደናንተው ዓሊም ነኝ የሚለውን ለማሳየት ወይም ቂሎችንና ደካማ ግንዛቤ ያላቸውን ልትሟገቱና ልታናግሩ ወይም በመድረኮች ግንባር ቀደም ለመሆንና ከሌላው ቅድሚያ እንዲሰጠው በማለም ዕውቀት ከመፈለግ ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን አስጠነቀቁ። ይህን የፈፀመ ሰው፤ ለአላህ ብሎ ዕውቀት በመፈለግ ላይ እሱ ለይዩልኝና ያለ ኢኽላስ በመስራቱ እሳት ይገባዋል።

فوائد الحديث

ዕውቀትን ሊፎካከርበት ወይም ሊሟገትበት ወይም በመድረኮች ቅድሚያ እንዲሰጠውና ለመሳሰሉት አላማዎች የተማረ ሰው በእሳት እንደተዛተበት፤

ዕውቀትን ለሚማርና ለሚያስተምር ሰው ኒያን ማጥራት አንገብጋቢነት ፤

ኒያ የሥራ መሰረት መሆኑንና ምንዳም በኒያ ላይ የተመረኮዘ መሆኑን ተረድተናል።

التصنيفات

የቀልብ በሽታዎች, ከዝንባሌና ስሜት ማውገዝ, Merit and Significance of Knowledge