እናንተ ሰዎች ሆይ! አላህ ከናንተ ላይ የድንቁርና ዘመንን ኩራትና በአባቶች መኮፈስን አስወግዷል።

እናንተ ሰዎች ሆይ! አላህ ከናንተ ላይ የድንቁርና ዘመንን ኩራትና በአባቶች መኮፈስን አስወግዷል።

ከኢብኑ ዑመር (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: "የአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) መካ የተከፈተ እለት ለሰዎች ኹጥባ አደረጉ። እንዲህም አሉ ' እናንተ ሰዎች ሆይ! አላህ ከናንተ ላይ የድንቁርና ዘመንን ኩራትና በአባቶች መኮፈስን አስወግዷል። ሰዎች ሁለት አይነት ናቸው። በጎ፣ አላህን ፈሪና አላህ ዘንድ የተከበረ፤ አመፀኛ፣ ጠማማና አላህ ዘንድ የወረደ ናቸው። ሰዎች የአደም ልጆች ናቸው። አላህም አደምን ከአፈር ነው የፈጠረው። አላህ እንዲህ ብሏል፦ {እናንተ ሰዎች ሆይ! እኛ ከወንድና ከሴት ፈጠርናችሁ። እንድትተዋወቁም ጎሳዎችና ነገዶች አደረግናችሁ። አላህ ዘንድ በላጫችሁ በጣም አላህን ፈሪያችሁ ነው። አላህ ግልፅን አዋቂ ውስጥንም አዋቂ ነው።} [ሑጁራት: 13]'"

[ሶሒሕ ነው።] [ቲርሚዚ ዘግበውታል።]

الشرح

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) መካ የተከፈተ እለት ለሰዎች ኹጥባ አደረጉ። እንዲህም አሉ፦ እናንተ ሰዎች ሆይ! አላህ ከናንተ ላይ የድንቁርናን ዘመን ኩራት፣ ትዕቢትንና በአባቶች መኮፈስን አስወግዷል። ሰዎች ሁለት አይነት ብቻ ናቸው። ወይ አማኝ፣ በጎ፣ አላህን ፈሪና ለአላህ ባሪያ የሆነ ነው። ይህ ግለሰብ ሰዎች ዘንድ የተከበረ ዘርና ጎሳ ባለቤት ባይሆን እንኳ አላህ ዘንድ የተከበረ ነው። ወይም ደግሞ ከሀዲ፣ አመፀኛና ጠማማ ነው። ይህም ስልጣንና ክብር ያለው ከተከበረ ዘር እንኳ ቢሆን አላህ ዘንድ ከምንም ነገር ጋር የማይስተካከል የተዋረደና የዘቀጠ ነው። ሰዎች ሁሉ የኣደም ልጆች ናቸው። አላህም ኣደምን ከአፈር ነው የፈጠራቸው። መሰረቱ ከአፈር የሆነ ደግሞ በራሱ ሊኮራና ሊደነቅ አይገባውም። የዚህም ማረጋገጫ እንዲህ የሚለው የአላህ ንግግር ነው፦ {እናንተ ሰዎች ሆይ! እኛ ከወንድና ከሴት ፈጠርናችሁ። እንድትተዋወቁም ጎሳዎችና ነገዶች አደረግናችሁ። አላህ ዘንድ በላጫችሁ በጣም አላህን ፈሪያችሁ ነው። አላህ ግልፅን አዋቂ ውስጥንም አዋቂ ነው።} [ሑጁራት: 13

فوائد الحديث

በዘርና በጎሳ መኩራራት መከልከሉን እንረዳለን።

التصنيفات

የኢስላም ደረጃና ውበቶቹ, የኢስላም ሃይማኖት በጥቅሉ, የሰው መብቶች በኢስላም, የአንቀፆች ተፍሲር (ማብራሪያ)