አላህ ለሱ መልካም የሻለትን ሰው ይፈትነዋል።

አላህ ለሱ መልካም የሻለትን ሰው ይፈትነዋል።

ከአቡ ሁረይራ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸው - እንዳስተላለፉት እንዲህ ብለዋል፦ የአላህ መልዕክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦ "አላህ ለሱ መልካም የሻለትን ሰው ይፈትነዋል።"

[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪ ዘግበውታል።]

الشرح

አላህ በአንድ አማኝ ባሪያው ላይ መልካምን የፈለገ ጊዜ በነፍሳቸው፤ በገንዘባቸውና በቤተሰቦቻቸው እንደሚፈትናቸው ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ተናገሩ። ይህም አንድ አማኝ በሱ ምክንያት ወደ አላህ በዱዓእ መጠጋት፣ የወንጀል መማርና የደረጃ ከፍ ማለትን ስለሚያገኝለት ነው።

فوائد الحديث

አማኝ የሆነ ሰው ለተለያዩ የመከራ አይነቶች የተጋለጠ ነው።

ፈተና የአንድ አማኝ ደረጃውን ከፍ ከማድረጉ፣ ማዕረጉን ከመስቀሉና ወንጀሉን ከማስማሩ አኳያ አላህ ለባሪያው ላለው ውዴታ ምልክት ሊሆን ይችላል።

በመከራዎች ላይ ትእግስት በማድረግና ባለመበሳጨት ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።

التصنيفات

የቀዷና ቀደር ጉዳዮች