إعدادات العرض
'አላህ ጥንቁቅ፣ (ከሰዎች) የተብቃቃና ድብቅ የሆነን ባሪያ ይወዳል።'
'አላህ ጥንቁቅ፣ (ከሰዎች) የተብቃቃና ድብቅ የሆነን ባሪያ ይወዳል።'
ከሰዕድ ቢን አቢ ወቃስ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል: "የአላህን መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ: 'አላህ ጥንቁቅ፣ (ከሰዎች) የተብቃቃና ድብቅ የሆነን ባሪያ ይወዳል።'"
[ሶሒሕ ነው።] [ሙስሊም ዘግበውታል።]
الترجمة
العربية বাংলা Bosanski English Español فارسی Français Bahasa Indonesia Русский Tagalog Türkçe اردو 中文 हिन्दी Tiếng Việt සිංහල Kurdî Hausa Português മലയാളം తెలుగు မြန်မာ ไทย Deutsch 日本語 پښتو অসমীয়া Shqip Svenska Čeština ગુજરાતી Yorùbá Nederlands ئۇيغۇرچە Kiswahili தமிழ் دری Fulfulde Magyar Italiano ಕನ್ನಡ Кыргызча Lietuvių Malagasy Română Kinyarwanda नेपाली Српски Wolof Soomaali Moore Українська Български Azərbaycan ქართული тоҷикӣ bm Oromoo Македонскиالشرح
ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም አላህ አንዳንድ ባሮቹን እንደሚወድ ገለፁ። ከነርሱም መካከል ፈሪሃ አላህ የሆነ አንዱ ነው። እርሱም:- የአላህን ትእዛዛት የሚተገብርና ክልከላዎቹን የሚርቅ ነው። ከሰዎች የተብቃቃንም ይወዳል። እርሱም:- በአላህ በመመካቱ የተነሳ ከሰዎች የተብቃቃና ከአላህ ውጪ ወደ ማንም የማይዞር ነው። ድብቅንም ይወዳል። እርሱም:- ለጌታው ባሪያና የሚተናነስ፣ በሚጠቅመው ነገር ላይ የሚጠመድ፣ ማንም እርሱን ማወቁም ይሁን ስለርሱ በሙገሳና ውዳሴ ማውራቱን ከቁብ የማይቆጥር ሰው ነው።فوائد الحديث
አላህ ባሮቹን እንዲወድ የሚያስፈርዱ አንዳንድ ባህሪያቶች መገለፃቸውን እንረዳለን። እነርሱም:- አላህን መፍራት፣ መተናነስና አላህ የሰጠንን ወደን መቀበል ነው።
التصنيفات
ምስጉን ስነ-ምግባር