إعدادات العرض
ሰይጣን አንዳችሁ ዘንድ በመምጣት "ይህን የፈጠረው ማነው? ይህንንስ የፈጠረው?" እያለ ይጠይቃችኋል "ጌታህንስ የፈጠረው ማነው?" ብሎ እስኪጠይቃችሁ ድረስ ይደርሳል፤ ይህ ጥያቄ የደረሰው…
ሰይጣን አንዳችሁ ዘንድ በመምጣት "ይህን የፈጠረው ማነው? ይህንንስ የፈጠረው?" እያለ ይጠይቃችኋል "ጌታህንስ የፈጠረው ማነው?" ብሎ እስኪጠይቃችሁ ድረስ ይደርሳል፤ ይህ ጥያቄ የደረሰው ጊዜ በአላህ ይጠበቅም ይከልከልም።
ከአቡ ሁረይራ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው፦ የአላህ መልክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ አሉ፦ "ሰይጣን አንዳችሁ ዘንድ በመምጣት "ይህን የፈጠረው ማነው? ይህንንስ የፈጠረው?" እያለ ይጠይቃችኋል "ጌታህንስ የፈጠረው ማነው?" ብሎ እስኪጠይቃችሁ ድረስ ይደርሳል፤ ይህ ጥያቄ የደረሰው ጊዜ በአላህ ይጠበቅም ይከልከልም።"
[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]
الترجمة
العربية English မြန်မာ Svenska Čeština ગુજરાતી Yorùbá Nederlands اردو Español Bahasa Indonesia ئۇيغۇرچە বাংলা Türkçe Bosanski සිංහල हिन्दी Tiếng Việt Hausa മലയാളം తెలుగు Kiswahili پښتو অসমীয়া Shqip دری Ελληνικά Български Fulfulde ಕನ್ನಡ Кыргызча Lietuvių or Română Kinyarwanda Српски тоҷикӣ O‘zbek नेपाली Moore Kurdî Oromoo Wolof Soomaali Français Tagalog Azərbaycan Українська bm தமிழ் Deutsch ქართული Português Македонски Magyar فارسی Русский 中文 km Malagasyالشرح
የአላህ መልክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ሰይጣን አማኞችን ለመጎትጎት ለሚያቀርባቸው ጥያቄዎች ፍቱን መድኃኒት ተናገሩ። "ይህን ማን ፈጠረው? ይህንንስ ማን ፈጠረው? ሰማይን ማን ነው የፈጠረው? ምድርንስ ማን ነው የፈጠረው?" በማለት ሰይጣን ጥያቄ ያቀርብልናል። አማኙም በእምነቱም ፣ በተፈጥሮውም፣ በአይምሮውም ተጠቅሞ "አላህ" በማለት ይመልስለታል። ሰይጣን ግን በዚህ የጉትጎታ ወሰን ላይ ከመቆም ይልቅ "ጌታህን ማን ፈጠረው?" ወደሚል የጉትጎታ ደረጃ ይሸጋገራል። በዚህ ጊዜ አንድ አማኝ ይህንን ጉትጎታ በሦስት ነገሮች ይከላከላል፦ በአላህ በማመን ከሰይጣን በአላህ በመጠበቅ ከጉትጎታው ጋር አብሮ መቀጠልን በማቆምفوائد الحديث
የሰይጣንን ጉትጎታና ውልታ ችላ ማለት፤ ስለ እሱ ማሰብ እንደማይገባ እና ይህን ለማስወገድ ወደ አላህ መጠጋት የሚገባ መሆኑን እንረዳለን።
ሁሉም በሰው ልጅ ቀልብ ውስጥ የሚከሰት ሸሪዐን ተፃራሪ የሆነ ጉትጎታ ከሰይጣን መሆኑን እንረዳለን።
በአላህ ማንነት ጉዳይ ማስተንተን መከልከሉና ስለፍጡራኑና አንቀፆቹ ማስተንተን ግን የተበረታታ ጉዳይ መሆኑን እንረዳለን።