إعدادات العرض
እኔ ከናንተ መካከል ፍፁም ወዳጅ ከመያዝ ወደ አላህ እጥራራለሁ። ምክንያቱም የላቀው አሏህ ኢብራሂምን ፍፁም ወዳጅ
እኔ ከናንተ መካከል ፍፁም ወዳጅ ከመያዝ ወደ አላህ እጥራራለሁ። ምክንያቱም የላቀው አሏህ ኢብራሂምን ፍፁም ወዳጅ
ከጁንዱብ ረዲየሏሁ ዐንሁ እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል፡ "ነብዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከመሞታቸው አምስት (ሌሊቶች) በፊት እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ፡- ' እኔ ከናንተ መካከል ፍፁም ወዳጅ ከመያዝ ወደ አላህ እጥራራለሁ። ምክንያቱም የላቀው አሏህ ኢብራሂምን ፍፁም ወዳጅ አድርጎ እንደያዘው ሁሉ እኔንም ፍፁም ወዳጅ አድርጎ ይዞኛልና። ከኡመቴ መካከል ፍፁም ወዳጅ አድርጌ የምይዝ ብሆን ኖሮ አቡበከርን ነበር ፍፁም ወዳጅ አድርጌ የምይዘው። አዋጅ! እነዚያ ከናንተ በፊት የነበሩት የነብያቶቻቸውንና የፃድቃኖቻቸውን መቃብር መስገጃ ስፍራ አድርገው ይይዙ ነበር። አዋጅ! መቃብርን መስገጃ ስፍራ አድርጋችሁ አትያዙ! እኔ እየከለከልኳችሁ ነው።'"
الترجمة
العربية বাংলা Bosanski English Español فارسی Français Bahasa Indonesia Русский Tagalog Türkçe اردو 中文 हिन्दी Kurdî Hausa Português മലയാളം తెలుగు Kiswahili தமிழ் မြန်မာ Deutsch 日本語 پښتو Tiếng Việt অসমীয়া Shqip Svenska Čeština ગુજરાતી Yorùbá Nederlands ئۇيغۇرچە සිංහල دری Akan Azərbaycan Български Fulfulde Magyar ಕನ್ನಡ Кыргызча Lietuvių नेपाली or Română Kinyarwanda тоҷикӣ O‘zbek Moore Wolof Oromoo bm Українська rn Српски ქართული Македонски Ελληνικά ភាសាខ្មែរ Malagasyالشرح
ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በአላህ ዘንድ ያላቸውን ደረጃ አሳወቁ፤ ልክ እንደ ኢብራሂም ዐለይሂ ሰላም እሳቸውም ላእላይ እርከን የደረሰ ውዴታ መጎናፀፋቸውንም ተናገሩ። ልባቸው በአላህ ውዴታ፣ ማላቅና ማወቅ ስለተሞላ ከአሏህ ውጭ ፍፁም ወዳጅ ሊኖራቸው እንደማይችልም ገለፁ። ከፍጡራን መካከል ፍፁም ወዳጅ የሚይዙ ቢሆኑ ኖሮ ያ ሰው አቡበከር አስሲዲቅ አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና ይሆን እንደነበረም ተናገሩ። ከዚያም አይሁዶችና ክርስቲያኖች የነቢያቶቻቸውንና የፃድቃኖቻቸውን መቃብር ከአላህ ውጪ ወደምትመለክ ጣኦታዊ የአምልኮ ስፍራ በመለወጥ እንዲሁም የፃድቃኖችና ነቢያቶች መቃብር ላይ መስገጃና ቤተ መቅደሶችን በመገንባት የፈፀሙትን ልክ ያለፈ የውዴታ ድንበር ከማለፍ አስጠነቀቁ። አስከትለውም ኡመታቸውም የነሱን አይነት ድርጊት እንዳይፈፅሙ ከለከሉ።فوائد الحديث
አቡበክር ሲዲቅ ረዲየሏሁ ዐንሁ ያላቸውን ደረጃ፤ ከሶሓቦችም ሁሉ በላጩ እርሳቸው መሆናቸውን፤ ከረሱል ዐለይሂ ሶላቱ ወሰላም በኋላ በርሳቸው የመሪነት ቦታ ለመተካት ይበልጥ የተገቡትም እርሳቸው መሆናቸውን እንረዳለን።
በመቃብር ላይ መስገጃ መገንባት ያለፉት ህዝቦች ከሚፈፅሟቸው ውግዝ ተግባራት መካከል ነው።
መቃብርን የአምልኮ ስፍራ አድርጎ መያዝ፣ መቃብር አጠገብም ሆነ ወደርሷ ዞሮ መስገድ፣ ወይም በላያቸው ላይ መስገጃ ወይም ጉልላት መስራት ወደ ሽርክ ሊያደርስ ስለሚችል ተከልክሏል።
በፃድቃን ላይ ድንበር ማለፍ ወደ ሽርክ ሊያደርስ ስለሚችል መጠንቀቅ ይገባል።
ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ከመሞታቸው አምስት ቀናት ቀደም ብለው ማስጠንቀቃቸው ያስጠነቀቁት ጉዳይ ያለውን አደገኝነት ያሳያል።