إعدادات العرض
ለተቸገረ (ባለዕዳ) ጊዜ የሰጠ ወይም ይቅር ያለ አላህ ከጥላው በስተቀር ጥላ በሌለበት የትንሳኤ ቀን ከዐርሹ ጥላ ስር ያስጠልለዋል።
ለተቸገረ (ባለዕዳ) ጊዜ የሰጠ ወይም ይቅር ያለ አላህ ከጥላው በስተቀር ጥላ በሌለበት የትንሳኤ ቀን ከዐርሹ ጥላ ስር ያስጠልለዋል።
ከአቡ ሁረይራ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸው - እንዳስተላለፉት እንዲህ ብለዋል፦ የአላህ መልዕክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦ "ለተቸገረ (ባለዕዳ) ጊዜ የሰጠ ወይም ይቅር ያለ አላህ ከጥላው በስተቀር ጥላ በሌለበት የትንሳኤ ቀን ከዐርሹ ጥላ ስር ያስጠልለዋል።"
[ሶሒሕ ነው።] [ቲርሚዚ ዘግበውታል።]
الترجمة
عربي বাংলা Bosanski English Español فارسی Français Bahasa Indonesia Русский Tagalog Türkçe اردو 中文 हिन्दी Kurdî Hausa Português മലയാളം తెలుగు Kiswahili தமிழ் မြန်မာ Deutsch 日本語 پښتو Tiếng Việt অসমীয়া Shqip Svenska cs ગુજરાતી Yorùbá Nederlands ئۇيغۇرچە සිංහල ไทย دری ff hu it kn Кыргызча Lietuvių mg or ro rw Soomaali Српски тоҷикӣ uz mos नेपालीالشرح
ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ለተበዳሪ የእዳ መክፈያ ጊዜውን ያዘገየለት ወይም ያለበትን እዳ ከሱ ላይ ይቅር ያለ ምንዳው፦ የትንሳኤ ቀን ፀሀይ ወደ ሰዎች አናት ቀርባ ሀሩሯ በነሱ ላይ በሚበረታበት ወቅት አላህ ከዐርሹ ስር እንደሚያስጠልላቸው ተናገሩ። አላህ ያስጠለለው ሰው ካልሆነ በስተቀር አንድም ሰው ጥላ አያገኝም።فوائد الحديث
ለአላህ ባሮች ነገሮችን የማቅለል ትሩፋቱ፤ እሱም ከትንሳኤ ቀን መከራዎች የመዳኛ ምክንያት ነው።
ምንዳ የሚሰጠን በስራችን ልክ ነው።
التصنيفات
የመጨረሻው ህይወት