إعدادات العرض
አይነአፋርነት ከኢማን ነው።
አይነአፋርነት ከኢማን ነው።
ከዐብደላህ ቢን ዑመር -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: "ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም አንድ ሰውዬ ወንድሙን በአይነአፋርነቱ ሲወቅሰው ሰሙና 'አይነአፋርነት ከኢማን ነው።' አሉት።
[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]
الترجمة
العربية বাংলা Bosanski English Español فارسی Français Bahasa Indonesia Русский Tagalog Türkçe اردو 中文 हिन्दी Tiếng Việt සිංහල Kurdî Hausa Português മലയാളം తెలుగు မြန်မာ ไทย Deutsch 日本語 پښتو অসমীয়া Shqip Svenska Čeština ગુજરાતી Yorùbá Nederlands ئۇيغۇرچە Kiswahili தமிழ் دری Fulfulde Magyar ಕನ್ನಡ Кыргызча Lietuvių or Română Kinyarwanda Српски O‘zbek Moore नेपाली Oromoo Wolof Soomaali Български Українська Azərbaycan ქართული тоҷикӣ Македонски bm Malagasyالشرح
ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም አንድን ሰውዬ ለወንድሙ አይነአፋርነት ማብዛት እንዲተው ሲመክረው ሰሙትና አይነአፋርነት ከኢማን መሆኑን እና ከመልካም በስተቀር ይዞ እንደማይመጣ ገለፁለት። አይነአፋርነት መልካም ድርጊት ለመስራትና እኩይ ተግባር ለመተው የሚያነሳሳ ስነምግባር ነው።فوائد الحديث
ከመልካም ተግባር የሚከለክል ባህሪ ተወዛጋቢነት፣ ደካማነት፣ ልፍስፍስነትና ፈሪነት እንጂ አይነአፋርነት አይባልም።
ከአሏህ ሓያእ ማድረግ የሚሆነው ትእዛዛትን በመፈፀምና ክልከላትን በመተው ነው።
ከፍጡራን ሐያእ ማድረግ የሚሆነው እነሱን በማክበር፣ በሚመጥናቸው ደረጃቸው ላይ በማስቀመጥና በተለምዶ ከሚያፀይፍ ድርጊት በመራቅ ነው።
التصنيفات
ምስጉን ስነ-ምግባር