إعدادات العرض
አንድ ሰው ወንድሙን ከወደደው እንደሚወደው ይንገረው።
አንድ ሰው ወንድሙን ከወደደው እንደሚወደው ይንገረው።
ከሚቅዳም ቢን መዕዲከሪብ እንደተላለፈው ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል: "አንድ ሰው ወንድሙን ከወደደው እንደሚወደው ይንገረው።"
[ሶሒሕ ነው።] [አቡዳውድ፣ቲርሚዚ፣ ነሳኢ በሱነኑል ኩብራ ፣ አሕመድ ዘግበውታል።]
الترجمة
العربية বাংলা Bosanski English Español فارسی Français Bahasa Indonesia Русский Tagalog Türkçe اردو 中文 हिन्दी Tiếng Việt Kurdî Hausa Português മലയാളം తెలుగు Kiswahili မြန်မာ Deutsch 日本語 پښتو অসমীয়া Shqip Svenska Čeština ગુજરાતી Yorùbá Nederlands ئۇيغۇرچە සිංහල தமிழ் ไทย دری Akan Azərbaycan Български Fulfulde Magyar Italiano ಕನ್ನಡ Кыргызча Lietuvių Malagasy नेपाली or Română Kinyarwanda тоҷикӣ O‘zbek Moore Wolof Oromoo Српски Soomaali bm Українська rn km ქართული Македонски mnkالشرح
ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በምእመናን መካከል መስተጋብራቸውን ከሚያጠናክሩና በመካከላቸውም ውዴታን ከሚያሰፍኑ ሰበቦች መካከል አንዱን ጠቀሱ። ይኸውም አንድ ሰው ወንድሙን የሚወደው ከሆነ እንደሚወደው ይንገረው አሉ።فوائد الحديث
ለዓለማዊ ጥቅም ሳይሆን ጥርት ባለ መልኩ ለአላህ ብሎ መውደድ ያለውን ደረጃ፤
መዋደዱና መግባባቱ እንዲጨምር ለአላህ ብለው የሚወዱትን እንደሚወዱት መንገር እንደሚበረታታ፤
በምእመናን መካከል መዋደድ መስፋፋቱ ኢማናዊ የሆነውን ወንድማማችነት እንደሚያጠነክርና ማህበረሰቡንም ከመለያየትና ከመበታተን እንደሚታደግ፤