በእውነተኝነት ላይ አደራችሁን! እውነተኝነት ወደ መልካም ይመራል። መልካም ነገር ደግሞ ወደ ጀነት ይመራልና።

በእውነተኝነት ላይ አደራችሁን! እውነተኝነት ወደ መልካም ይመራል። መልካም ነገር ደግሞ ወደ ጀነት ይመራልና።

ከዐብደላህ ቢን መስዑድ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድለላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል: "በእውነተኝነት ላይ አደራችሁን! እውነተኝነት ወደ መልካም ይመራል። መልካም ነገር ደግሞ ወደ ጀነት ይመራልና። ሰውዬው አላህ ዘንድ እውነተኛ ተብሎ እስኪፃፍ ድረስ እውነት ከመናገርና እውነትን ከመምረጥ አይወገድም። አደራችሁን ውሸትን ተጠንቀቁ! ውሸት ወደ ጥመት ይመራል። ጥመት ደግሞ ወደ እሳት ይመራልና። ሰውዬው አላህ ዘንድ ውሸታም ተብሎ እስኪፃፍ ድረስ ከመዋሸትና ለውሸት ከመጣር አይወገድ።"

[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]

الشرح

ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እውነተኝነትን አዘዙ። እውነተኝነትን አጥብቆ መያዝ ለዘውታሪ መልካም ስራና በመልካም ስራ ላይም እንዲዘወትር የሚያደርገው በመሆኑ ሰውዬውን ወደ ጀነት እንደሚያደርሰው ተናገሩ። ሰውዬው እውነት መናገርን በድብቅም ይሁን በይፋ ከመደጋገም እስካልተወገደ እጅግ እውነተኛ የሚል ስያሜ እስኪገባው ይደርሳል። ይህም በእውነተኝነት ላይ ጫፍ የደረሰ ሰው ማለት ነው። ቀጥለውም ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከውሸትና ከቅጥፈት ንግግር አስጠነቀቁ። ይህም ከቀጥተኛው መንገድ ወደ መጣመም፣ ለክፋትና ለወንጀል ስለሚያነሳሳ ነው። ከዚያም ወደ እሳት ያደርሰዋል። ሰውዬውም ውሸትን ከማብዛት እስካልተወገደ ድረስ አላህ ዘንድ ውሸታም ተብሎ ይፃፋል።

فوائد الحديث

እውነተኝነት በጥረትና በትግል የሚገኝ የተከበረ ባህሪ ነው። ሰውዬው እውነት የርሱ ባህሪና ተፈጥሮው እስኪሆን ድረስ እውነት ከመናገርና ለእውነትም ከመጣር አይወገድም።

ውሸት ሰውዬው ባህሪውና መገለጫው እስኪሆንና ቀጥሎም አላህ ዘንድ ከውሸታሞች እስኪፃፍ ድረስ በመላመድ ብዛትና በንግግሩና በተግባሩ የሚያመጣው የተወገዘ ስነምግባር ነው።

እውነት የሚለው ቃል በምላስ ለሚነገር እውነት ስያሜው ይሰጣል፤ ይህም የውሸት ተቃራኒ ነው። በኒያ ለሚኖር እውነትም ስያሜው ይሰጣል፤ ይህም ስራን ለአላህ ማጥራት (ኢኽላስ) ተብሎ ይጠራል። በነየተው መልካም ነገር ላይ ላለው እውነተኛ ቁርጠኝነትም ስያሜው ይሰጣል። በተግባር ለሚኖር እውነተኝነትም የሚሰጥ ሲሆን ለዚህም ቢያንስ ውስጡና ውጪው እኩል መሆን አለባቸው። ስያሜው በተለያዩ ሁኔታዎች ላይ እውነተኛነትን ለመላበስም ይሰጣል። ለምሳሌ አላህን በመፍራት፣ አላህን በመከጀልና በሌሎችም ሁኔታዎች እውነተኛ መሆንን ሁሉ ያጠቃልላል። በዚህ መልኩ እውነትን የተላበሰ እጅግ እውነተኛ (ሲዲቅ) ይባላል። በተወሰኑት ብቻ እውነተኛ ከሆነ ግን እውነተኛ ብቻ ነው የሚባለው።

التصنيفات

ምስጉን ስነ-ምግባር