إعدادات العرض
አንዳችሁ መስጂድ የገባ ጊዜ ከመቀመጡ በፊት ሁለት ረከዓ ይስገድ።
አንዳችሁ መስጂድ የገባ ጊዜ ከመቀመጡ በፊት ሁለት ረከዓ ይስገድ።
ከአቡ ቀታዳ አስሰለሚይ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: የአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል: "አንዳችሁ መስጂድ የገባ ጊዜ ከመቀመጡ በፊት ሁለት ረከዓ ይስገድ።"
[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]
الترجمة
العربية English မြန်မာ Svenska Čeština ગુજરાતી Yorùbá Nederlands اردو Bahasa Indonesia ئۇيغۇرچە বাংলা Türkçe සිංහල हिन्दी Tiếng Việt Hausa Kiswahili پښتو অসমীয়া دری Кыргызча Lietuvių Kinyarwanda Українська नेपाली മലയാളം తెలుగు Bosanski ಕನ್ನಡ Kurdî Română Soomaali Shqip Српски Wolof Tagalog Moore தமிழ் Azərbaycan فارسی ქართული 中文 Magyar Português Deutsch Русский Македонски bm Malagasy Oromoo ភាសាខ្មែរالشرح
በማንኛውም ወቅትና ለማንኛውም አላማ መስጂድ የመጣና የገባ ሰው ከመቀመጡ በፊት ሁለት ረከዓ እንዲሰግድ ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) አነሳሱ። ይኸውም ሁለቱ የተሒየተል መስጂድ ረከዓዎች ናቸው።فوائد الحديث
ከመቀመጥ በፊት የተሒየተል መስጂድ ሁለት ረከዓ መስገድ እንደሚወደድ እንረዳለን።
ይህ ትእዛዝ መቀመጥ ለፈለገ ሰው ነው። መስጂድ ገብቶ ሳይቀመጥ የወጣን ሰው ትእዛዙ አይመለከተውም።
አንድ ሰጋጅ ሰዎች ሶላት ውስጥ ሆነው መስጂድ ቢገባና ቀጥታ እነርሱ ወደሚሰግዱት ሶላት ቢገባ ከሁለቱ የተሒየተል መስጂድ ረከዓ ያብቃቃዋል።