አሏህ ሆይ! ቀብሬን ጣኦት

አሏህ ሆይ! ቀብሬን ጣኦት

አቢ ሁረይራ ረዲየሏሁ ዐንሁ ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ማለታቸውን አስተላልፏል፡ "አሏህ ሆይ! ቀብሬን ጣኦት አታድርግብኝ፤ የነቢያቶቻቸውን መቃብር መስገጃ አድርገው በያዙ ህዝቦች ላይ የአሏህ እርግማን ሰፈነባቸው።"

[ሶሒሕ ነው።] [አሕመድ ዘግበውታል።]

الشرح

ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ቀብራቸውን በማላቅና የሱጁድ አቅጣጫውን ወደዛው በማድረግ ሰዎች እንደሚያመልኩት ጣኦት እንዳያደርግባቸው አምላካቸውን ተማፀኑ፤ ከዚያም የነቢያቶችን መቃብር የአምልኮ ስፍራ አድርገው በሚይዙ ላይ የአሏህ እርግማን እንደሰፈነባቸውና ከእዝነቱም እንዳባረራቸው አሳወቁ። ምክንያቱም መቃብሩን የአምልኮ ስፍራ አድርጎ መያዝ የቀብሩን ባለቤት እንዲመለክ ለማድረግና በተቀበረበት አካል ዙርያ አጉል እምነት ለማሳደር መዳረሻ ነውና።

فوائد الحديث

የነብያትና የጻድቃን ሰዎች መቃብርን በተመለከተ ሸሪዓው ያስቀመጠውን ገደብ ማለፉ ከአላህ ሌላ የሚመለኩ ጣኦት እንዲሆኑ ስለሚያደርጋቸው ወደ ሽርክ (ሽርክ) ከሚመሩ መንገዶች መጠንቀቅ እንደሚገባ፤

የተቀበረበት አካል ወደ አሏህ ምንም አይነት ቅርበት ቢኖረውም ቀብሩን ለማላቅም ይሁን በመቃብሩ አሏህን ለማምለክ ማለም እንደማይፈቀድ፤

መስገጃን መቃብር ላይ መገንባት የተከለከለ መሆኑን፤

ሶላተል ጀናዛ ላልተሰገደበት ሰው ሊሰግዱበት ካልሆነ በቀር መስጂድ ባይገነቡም መቃብር ዘንድ መስገድ የተከለከለ መሆኑን እንረዳለን።

التصنيفات

ማጋራት (ሺርክ), ማጋራት (ሺርክ), የመስጊዶች ህግጋት, የመስጊዶች ህግጋት