إعدادات العرض
ሰውዬው በጓደኛው ሃይማኖት ላይ ነው። አንዳችሁ የሚጎዳኘውን ሰው ይመልከት።
ሰውዬው በጓደኛው ሃይማኖት ላይ ነው። አንዳችሁ የሚጎዳኘውን ሰው ይመልከት።
ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው : ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል: "ሰውዬው በጓደኛው ሃይማኖት ላይ ነው። አንዳችሁ የሚጎዳኘውን ሰው ይመልከት።"
[ሐሰን ነው።] [አቡዳውድ፣ ቲርሚዚና አሕመድ ዘግበውታል።]
الترجمة
العربية বাংলা Bosanski English Español فارسی Français Bahasa Indonesia Русский Tagalog Türkçe اردو 中文 हिन्दी Hausa Kurdî Kiswahili Português සිංහල অসমীয়া ગુજરાતી Tiếng Việt Nederlands Soomaali नेपाली پښتو Svenska ไทย മലയാളം Кыргызча Română Oromoo తెలుగు ಕನ್ನಡ Српски ქართული Moore Kinyarwanda Magyar Македонски Čeština Lietuvių Українська Wolof Azərbaycanالشرح
ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የሰው ልጅ ፍፁም ጓደኛውንና ባልደረባውን በልማዱና ኑሮው እንደሚመሳሰል፤ ጓደኝነትም በስነምግባር፣ በባህሪና የኑሮ ዘይቤ ላይ ተፅዕኖ እንደሚያሳድር ገለፁ። ለዚህም ጥሩ ጓደኛ ወደ ኢማን፣ ቅናቻና መልካም ነገር ይጠቁማልም ለባልደረባውም አጋዥ ይሆናልና ጓደኛ አመራረጣችንን እንድናሳምር ጠቆሙ።فوائد الحديث
መልካሞችን በመወዳጀትና በመምረጥ መታዘዙን፤ መጥፎዎችን መወዳጀት ደግሞ መከልከሉን እንረዳለን።
ከዘመድ ይልቅ ጓደኛን ብቻ ለይተው መጥቀሳቸው ጓደኛ አንተ ራስህ የምትመርጠው ስለሆነ፤ ወንድምና ቅርብ ዘመድ ግን አንተ ምንም ምርጫ ስለሌለህ ነው።
ጓደኛን መያዝ የግድ ጥናት ካደረግክ በኋላ መሆን አለበት።
አንድ ሰው አማኞችን በመወዳጀት ዲኑን እንደሚያጠነክርና አመፀኞችን በመወዳጀት ደግሞ እንደሚያደክመው እንረዳለን።
التصنيفات
የመወዳጀትና የመራራቅ ህግጋት