إعدادات العرض
አዋጅ! ከእኔ የሆነ ሐዲሥ በአልጋው ላይ ወደተደገፈ አንድ ሰውዬ ይደርሰውና፡ "በእኛና በእናንተ መካከል (የሚዳኘን) የአላህ መጽሐፍ ነው
አዋጅ! ከእኔ የሆነ ሐዲሥ በአልጋው ላይ ወደተደገፈ አንድ ሰውዬ ይደርሰውና፡ "በእኛና በእናንተ መካከል (የሚዳኘን) የአላህ መጽሐፍ ነው
አልሚቅዳም ቢን መዕዲከሪብ - አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና - እንዲህ አሉ፡- “የአላህ መልክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል፡- "አዋጅ! ከእኔ የሆነ ሐዲሥ በአልጋው ላይ ወደተደገፈ አንድ ሰውዬ ይደርሰውና፡ "በእኛና በእናንተ መካከል (የሚዳኘን) የአላህ መጽሐፍ ነው። በውስጡ የተፈቀደ ሆኖ ያገኘነውን (ብቻ) እንደ ሐላል እንቆጥረዋለን በውስጡም ሐራም ሆኖ ያገኘነውን (ብቻ) እንደ ሐራም እንቆጥረዋለን።" የሚልበት ወቅት ቅርብ ነው። በእርግጥ የአላህ መልክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ሐራም (እርም) ያደረጉት ማንኛውም ነገር አላህ ሐራም እንዳደረገው ነው።'”
الترجمة
العربية Kurdî English Kiswahili Español اردو Português বাংলা Bahasa Indonesia فارسی தமிழ் हिन्दी සිංහල Tiếng Việt മലയാളം Русский မြန်မာ ไทย پښتو অসমীয়া Shqip Svenska Čeština ગુજરાતી Yorùbá Nederlands ئۇيغۇرچە Türkçe Bosanski Hausa తెలుగు دری Ελληνικά Български Fulfulde ಕನ್ನಡ Кыргызча Lietuvių or Română Kinyarwanda Српски тоҷикӣ O‘zbek नेपाली Moore Oromoo Wolof Tagalog Soomaali Français Azərbaycan Українська bm ქართული Deutsch Македонски Magyar 中文 kmالشرح
ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ከሰዎች መካከል የተወሰኑ ሰዎች አንድ ፍራሹ ላይ የተደገፈ ሰው፥ ከነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ሐዲሥ ሲደርሰው "በጉዳዮቻችን ላይ በእኛና በናንተ መካከል የሚዳኘን የተከበረው ቁርኣን ነው፤ እሱ በቂያችን ነው፤ በቁርኣን ውስጥ ያገኘነውን ሐላሎች (ፍቁድ) እንሰራበታለን፤ ቁርኣን ውስጥ ያገኘነውን ሐራሞች (እርሞች) እንርቀዋለን። " የሚልበት ዘመን እንደቀረበ ተናገሩ። ቀጥለው ሁሉም በሱናቸው (ሀዲሳቸው) እርም ያደረጉት ወይም የከለከሉት ነገር ደረጃው ልክ አላህ በቁርኣኑ እንደከለከለው አምሳያ እንደሆነ ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና አብራሩ። ምክንያቱም እሳቸው የጌታቸውን መልዕክት አድራሽ ናቸውና።فوائد الحديث
ቁርኣን እንደሚከበረውና ከሱ ድንጋጌዎች እንደሚወሰደው ሁሉ ሱናንም ማላቅ እንደሚገባ እንረዳለን።
መልክተኛውን መታዘዝ አላህን መታዘዝ ነው፤ እሳቸውንም አለመታዘዝ አላህን አለመታዘዝ ነው።
የሐዲሥ ማስረጃነት የፀና መሆኑና ሐዲሥን የማይቀበል ወይም የሚያወግዝ ሰው ላይ በቂ ምላሽ መሰጠቱን እንረዳለን።
ከሐዲሥ በማፈንገጥ በቁርኣን ብቻ መብቃቃትን የሞገተ ሰው፥ በሁለቱም ላይ ያፈነገጠና ቁርኣንን እከተላለሁ የሚለው ሙግቱም ቅጥፈት እንደሆነ ያስረዳል።
የነቢዩን የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ነቢይነት ከሚጠቁሙ ነገሮች መካከል ለወደፊት ይከሰታል ብለው የተናገሩት ነገር እንደተናገሩት መከሰቱ ነው።