إعدادات العرض
1- አዋጅ! ከእኔ የሆነ ሐዲሥ ወደ አንዱ በአልጋው ላይ እንደተደገፈ ይደርሰውና፡ "በእኛና በእናንተ መካከል (የሚዳኘን) የአላህ መጽሐፍ ነው
2- እነርሱ እየተቀጡ ነው። (በናንተ እይታ) ትልቅ በሆነ ወንጀልም አይደለም የሚቀጡት። አንደኛቸው ከሽንት አይጥራራም ነበር። ሌላኛው ደግሞ ነገር በማመላለስ የሚዞር ነበር።
3- ከሰዓቲቱ (ቂያማ) ምልክቶች መካከል ዕውቀት ይነሳል፣ መሀይምነት ይስፋፋል፣ ዝሙት ይበረክታል፣ አስካሪ መጠጥ መጠጣት ይበዛል፣ ለሀምሳ ሴቶች አንድ (ወንድ) አስተዳዳሪ እስኪሆን ድረስ ወንዶች አንሰው ሴቶች ይበዛሉ።
4- አንድ ሰው በአንድ ሰው ቀብር በኩል እያለፈ 'ዋ ምኞቴ ምናለ በርሱ ስፍራ ላይ እኔ በነበርኩ!' እስኪል ድረስ ሰአቲቱ አትቆምም።
5- አይሁዶችን ሳትዋጉና ከኋላው አንድ አይሁድ የተደበቀበት ድንጋይ ሙስሊሙ ሆይ! ይህ አይሁድ ከኋላዬ አለ ግደለው ሳይል ሰዓቲቱ አትቆምም።
6- ነፍሴ በእጁ በሆነው ጌታ እምላለሁ። በናንተ ውስጥ የመርየም ልጅ ፍትሃዊ ዳኛ በቅርቡ ሆኖ ይወርዳል። መስቀልን ይሰባብራል፣ አሳማን ይገድላል፣ ግብርን ያነሳል፣ አንድም ሰው እስከማይቀበለው ድረስም ገንዘብ (ሀብት) ይበዛ።
7- ፀሀይ በመግቢያዋ እስክትወጣ ድረስ ሰዓቲቱ አትቆምም። ከመግቢያዋ የወጣችና ሰዎች የተመለከቷት ጊዜ ሁሉም ያምናሉ
8- ዘመኑ እስኪጣበብ ድረስ ሰአቲቱ አትቆምም።
9- ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን አንድ ነገር ካወሱ በኋላ እንዲህ አሉ: "ይህ የሚከሰተውም ዕውቀት ሊጠፋ የቀረበ ጊዜ ነው።
10- በመጨረሻዎቹ ሕዝቦቼ (ኡመቴ) ውስጥ እናንተም ሆነ አባቶቻችሁ ያልሰማችሁትን የሚነግሯችሁ ሰዎች ይመጣሉ። አደራችሁን አደራችሁን ተጠንቀቋቸው።