ቤቶቻችሁን መቃብር አታድርጉ። ሰይጣን የበቀራህ ምእራፍ የሚቀራበት ቤትን ይሸሻል።

ቤቶቻችሁን መቃብር አታድርጉ። ሰይጣን የበቀራህ ምእራፍ የሚቀራበት ቤትን ይሸሻል።

ከአቡ ሁረይራ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ አሉ: "ቤቶቻችሁን መቃብር አታድርጉ። ሰይጣን የበቀራህ ምእራፍ የሚቀራበት ቤትን ይሸሻል።"

[ሶሒሕ ነው።] [ሙስሊም ዘግበውታል።]

الشرح

ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ቤቶችን ከሶላት አራቁቶ እንደመቃብር የማይሰገድበት ማድረግን ከለከሉ። በመቀጠልም ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ሰይጣን የበቀራህ ምእራፍ ከሚቀራበት ቤት እንደሚሸሽ ተናገሩ።

فوائد الحديث

ቤት ውስጥ ሱና ሶላቶችን የመሰሉ አምልኮዎችን ማብዛት እንደሚወደድ እንረዳለን።

ወደ ሺርክና በተቀባሪው ላይ ወሰን ወደ ማለፍ ከሚያዳርሱ መንገዶች አንዱ ስለሆነ ከጀናዛ ሶላት በስተቀር መቃብር ግቢ ውስጥ ሶላት መስገድ አይፈቀድም።

መቃብር ዘንድ መስገድ መከልከሉ ሶሐቦች ዘንድ የተረጋገጠ ጉዳይ ስለሆነ ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ቤቶችን ልክ እንደመቃብር የማይሰገድባቸው ከማደረግ ከለከሉ።

التصنيفات

የምእራፎችና አንቀጾች ትሩፋቶች