ለአዛኞች አዛኙ ጌታ ያዝንላቸዋል። ለምድር ነዋሪዎች እዘኑላቸው በሰማይ ያለው (አላህ) ያዝንላቹሀል።

ለአዛኞች አዛኙ ጌታ ያዝንላቸዋል። ለምድር ነዋሪዎች እዘኑላቸው በሰማይ ያለው (አላህ) ያዝንላቹሀል።

ከዐብደላህ ቢን ዐምር (ረዲየላሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ አሉ: "ለአዛኞች አዛኙ ጌታ ያዝንላቸዋል። ለምድር ነዋሪዎች እዘኑላቸው በሰማይ ያለው (አላህ) ያዝንላቹሀል።"

[ሶሒሕ ነው።] [ቲርሚዚ ዘግበውታል።]

الشرح

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እነዚያ ለሌሎች የሚያዝኑ አዛኙ ጌታ ሁሉን ነገር በሰፋው እዝነቱ እንደሚያዝንላቸው ገለፁ። ይህም ከሰሩት ጋር የገጠመ ምንዳ ነው። ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ቀጥለው በምድር ላይ ለሚኖር ለሰውም፣ ለእንስሳም፣ ለበራሪም ሆነ ለሌላ ማንኛውም አይነት ፍጡር ባጠቃላይ ማዘንን አዘዙ። የዚህ ምንዳም ከሰማያቱ በላይ ያለው አላህ ያዝንላቹሀል።

فوائد الحديث

የእስልምና ሀይማኖት የእዝነት ሀይማኖት ነው። የኢስላም ሁለመናው አላህን በመታዘዝና ለፍጡራን መልካም በማድረግ ላይ የቆመ ነው።

የላቀው አላህ በእዝነት ባህሪ የሚገለፅ ነው። ጥራት የተገባው አላህ አዛኝ ሩህሩህ ነው። ወደ ባሮቹ እዝነቱን የሚያደርስ ጌታ ነው።

ምንዳ የሚመነዳው በስራው አይነት ነውና ለአዛኞች አላህ ያዝንላቸዋል።

التصنيفات

አላህን በስሞቹና በባህሪያቱ መነጠል, ምስጉን ስነ-ምግባር