ሁለቱን ቀዝቃዛ ወቅቶች ሶላት የሰገደ ሰው ጀነት ገባ።

ሁለቱን ቀዝቃዛ ወቅቶች ሶላት የሰገደ ሰው ጀነት ገባ።

ከአቡ ሙሳ አልአሽዐሪይ (ረዲየላሁ ዐንሁ) -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና-እንደተላለፈው የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል፡ "ሁለቱን ቀዝቃዛ ወቅቶች ሶላት የሰገደ ሰው ጀነት ገባ።"

[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]

الشرح

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የሁለቱን ቀዝቃዛ ወቅቶች ሶላት ለመስገድ በመጣር ላይ አነሳሱ። እነሱም: የፈጅርና የዐስር ሶላቶች ናቸው። በጊዜው፣ በጀመዓና ሌሎቹንም የሶላት ሐቆች አሟልቶ እነዚህን ሶላቶች የሰገደ ሰውን ጀነት መግቢያ ሰበብ እንደሚሆኑት በመንገር አበሰሩ።

فوائد الحديث

የፈጅርና የዐስር ሶላት ላይ መጠባበቅ ያለውን ትሩፋት እንረዳለን። የፈጅር ሶላት ጣፋጭ እንቅልፍ የሚኖርበት ወቅት ሲሆን ዐስር ደግሞ ሰዎች በስራ የሚጠመዱበት ወቅት ነው። እነዚህን ሶላቶች ተጠባብቆ የሰገደ ሰው ሌሎቹንም ሶላቶች ተጠባብቆ መስገዱ አይቀርም።

የፈጅርና የዐስር ሶላት በቀዝቃዛ ወቅት የተሰየሙት የፈጅር ሶላት የምሽት ቅዝቃዜ ያለባት ወቅት ስለሆነ ሲሆን የዐስር ሶላት ደግሞ የቀኑ ቅዝቃዜ ስላለባት ነው። በሙቀት ወቅት ብትሆንም እንኳ ሙቀቷ ከርሷ በፊት ካለው ሙቀት አንፃር ቀዝቀዝ ያለ ነው። ወይም በዚህ የተሰየመው በማቆረኘት መልኩ ነው። ልክ ለፀሀይና ለጨረቃ ሁለቱ ጨረቃዎች እንደሚባለው ማለት ነው።

التصنيفات

የሶላት ትሩፋት