إعدادات العرض
በቃል ኪዳን ስር ያለን (ሙዓሀድን) የገደለ ሰው የጀነትን ሽታ አያሸትም። የጀነት ሽታዋ የሚገኘው አርባ አመት ከሚያስኬድ ርቀት በኋላ ነው።
በቃል ኪዳን ስር ያለን (ሙዓሀድን) የገደለ ሰው የጀነትን ሽታ አያሸትም። የጀነት ሽታዋ የሚገኘው አርባ አመት ከሚያስኬድ ርቀት በኋላ ነው።
ከዐብደሏህ ቢን ዓምር (ረዲየሏሁ ዓንሁማ) አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል፡ "በቃል ኪዳን ስር ያለን (ሙዓሀድን) የገደለ ሰው የጀነትን ሽታ አያሸትም። የጀነት ሽታዋ የሚገኘው አርባ አመት ከሚያስኬድ ርቀት በኋላ ነው።"
[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪ ዘግበውታል።]
الترجمة
العربية Bosanski English فارسی Français Русский हिन्दी Bahasa Indonesia 中文 বাংলা اردو Español Kurdî Português മലയാളം తెలుగు Kiswahili தமிழ் සිංහල မြန်မာ ไทย 日本語 پښتو Tiếng Việt অসমীয়া Shqip Svenska Čeština ગુજરાતી Yorùbá Nederlands ئۇيغۇرچە Türkçe Hausa دری Кыргызча Lietuvių Kinyarwanda नेपाली or ಕನ್ನಡ Română Soomaali Српски Wolof Українська Tagalog Moore Azərbaycan ქართული Magyar mr Deutsch Македонски bm Malagasy Oromoo ភាសាខ្មែរالشرح
ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሙዓሀድን በገደለ ሰው ላይ ያለበትን ከባድ ዛቻ ገለፁ። ሙዓሀድ ማለት ከከሀዲያን መካከል በቃል ኪዳንና በደህንነት ከለላ ወደ ኢስላም ሀገር የገባ ነው። እሱን የገደለ የጀነትን ሽታ አያሸትም። የጀነት ሽታ የሚገኘው አርባ አመት ከሚያስኬድ ርቀት ነው።فوائد الحديث
ከከሀዲያን መካከል "ሙዓሀድን" ፣ "ዚሚይን" እና "ሙስተእመንን" መግደል ክልክልና ከትላልቅ ወንጀል የሚመደብም ነው።
"ሙዓሀድ" ማለት: ከከሀዲያን መካከል በሀገሩ እየኖረ ሙስሊሞችን ላይዋጋ እነሱም ላይዋጉት ከሙስሊሞች ጋር ቃል ኪዳን የተጋባ ነው።
"ዚሚይ" ማለት: በሙስሊሞች ሀገር እንደሀገሩ እየኖረ ግብር የሚከፍል ነው።
"ሙስተእመን" ማለት ደግሞ ለተወሰነ ወቅት በቃል ኪዳንና ደህንነት ከለላ ወደ ሙስሊሞች ሀገር የገባ ሰው ነው።
ከሙስሊሞች ውጪ ካሉ ጋር ቃል ኪዳንን ማፍረስ መከልከሉን እንረዳለን።