إعدادات العرض
እኔ ሐውድ (ኩሬ) ላይ ሁኜ ከናንተ መካከል ወደ እኔ የሚመጣን እመለከታለሁ። በአቅራቢያዬ ያሉ ሰዎች (እንዳይጠጡ) ይያዛሉ። እኔም "ጌታዬ ከኔ ከኡመቴ ናቸው’እኮ
እኔ ሐውድ (ኩሬ) ላይ ሁኜ ከናንተ መካከል ወደ እኔ የሚመጣን እመለከታለሁ። በአቅራቢያዬ ያሉ ሰዎች (እንዳይጠጡ) ይያዛሉ። እኔም "ጌታዬ ከኔ ከኡመቴ ናቸው’እኮ
አስማእ ቢንት አቢበክር -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንዲህ አሉ፦ ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦ "እኔ ሐውድ (ኩሬ) ላይ ሁኜ ከናንተ መካከል ወደ እኔ የሚመጣን እመለከታለሁ። በአቅራቢያዬ ያሉ ሰዎች (እንዳይጠጡ) ይያዛሉ። እኔም "ጌታዬ ከኔ ከኡመቴ ናቸው’እኮ" እላለሁ። ለኔም፦ "ከአንተ ህልፈት በኋላ የሠሩትን ታውቃለህን? በአላህ እምላለሁ (ከእምነታቸው) ወደ ኋላ ከማፈግፈግ አልተወገዱም።" እባላለሁ።"
[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]
الترجمة
العربية English မြန်မာ Svenska Čeština ગુજરાતી Yorùbá Nederlands اردو Español Bahasa Indonesia ئۇيغۇرچە বাংলা Bosanski සිංහල हिन्दी Tiếng Việt Hausa മലയാളം తెలుగు Kiswahili پښتو অসমীয়া Shqip دری Ελληνικά Български Fulfulde ಕನ್ನಡ Кыргызча Lietuvių or Română Kinyarwanda Српски тоҷикӣ O‘zbek नेपाली Moore Kurdî Wolof Soomaali Français Azərbaycan Tagalog Українська தமிழ் Bambara Deutsch ქართული Português Македонски Magyar فارسی Русский 中文 ភាសាខ្មែរ Malagasy Oromoo ไทย मराठी ਪੰਜਾਬੀ Türkçe Lingala Italianoالشرح
ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን የትንሳኤ ቀን ከኡመታቸው መካከል ወደ ኩሬያቸው የሚመጣን ሰው ለመመልከት ከኩሬያቸው ላይ እንደሚሆኑ ገለፁ። ከሳቸው አቅራቢያም ሰዎች እንዳይጠጡ ይያዛል። እርሳቸውም፦ "ጌታዬ ሆይ እነሱ ከኔ ኡመት እኮ ናቸው" ይላሉ። ለርሳቸውም፦ "አንተን ከተለያዩ በኋላ የሰሩትን ታውቃለህን? በአላህ እምላለሁ ወደኋላቸው ከመመለስና ከእምነታቸው ከማፈንገጥ አልተወገዱም። ከአንተም አይደሉም ከኡመትህም አይደሉም።" ተብሎ ይመለስላቸዋል።فوائد الحديث
ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ለኡመታቸው ያላቸው እዝነትና ስለ ተከታዮቻቸው ያላቸው ጉጉት፤
ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን የነበሩበትን መንገድ መቃረን አደገኝነት፤
የነቢዩን የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ሱና አጥብቆ በመያዝ ላይ መነሳሳቱን ተረድተናል።