ሙስሊም ማለት ሙስሊሞች ከምላሱና እጁ (ክፋት) ሰላም የሆኑበት ነው፤ ሙሃጂር (ስደተኛ) ማለት አላህ የከለከለውን የተወ ነው።

ሙስሊም ማለት ሙስሊሞች ከምላሱና እጁ (ክፋት) ሰላም የሆኑበት ነው፤ ሙሃጂር (ስደተኛ) ማለት አላህ የከለከለውን የተወ ነው።

ከዐብደላህ ቢን ዐምር (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው : ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል: "ሙስሊም ማለት ሙስሊሞች ከምላሱና እጁ (ክፋት) ሰላም የሆኑበት ነው፤ ሙሃጂር (ስደተኛ) ማለት አላህ የከለከለውን የተወ ነው።"

[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]

الشرح

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እስልምናው የተሟላ ሙስሊም የሚባለው ሙስሊሞች ከምላሱ ሰላም የሆኑበት ሰው እንደሆነ ተናገሩ። ስለዚህም አይሰድባቸውምም፤ አይረግማቸውምም፤ አያማቸውምም፤ በሙስሊሞች መካከል በምላስ ከሚመጡ ማናቸውም የክፋት አይነት በየትኛውም ሊጎዳቸው አይሮጥም። ከእጁም ሙስሊሞች ሰላም የሆኑበት ነው። ስለዚህም በነርሱ ላይ ወሰን አያልፍም፤ ያለ አግባብ ገንዘባቸውን አይወስድምም በሌሎች መሰል ሁኔታዎችም ሙስሊሞችን አይጎዳም። ሙሃጂር ማለት: አላህ ክልክል ያደረገውን የተወ ነው።

فوائد الحديث

የኢስላም ምሉዕነት ሌሎች ላይ ቁሳዊም ሆነ ሞራላዊ ጉዳትን ባለማድረስ ካልሆነ በቀር አይረጋገጥም።

ምላስና እጅን ብቻ በማውሳት መገደቡ በነርሱ ምክንያት የሚደርስ ጉዳትና ጥፋቶች ስለሚበዙ ነው። ምክንያቱም አብዛኞቹ ክፋቶች የሚመነጩት ከሁለቱ ነውና።

ወንጀልን በመተው ላይና አላህ ያዘዘውን ነገር አጥብቆ በመያዝ ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።

በላጩ ሙስሊም የሚባለው የአላህን ሐቆችና የሙስሊሞችን ሐቅ የተወጣ ነው።

ወሰን አላፊነት በንግግር ወይም በተግባር ሊሆን ይችላል።

የተሟላ ሂጅራ የሚባለው አላህ ክልክል ያደረገውን በመተው ነው።

التصنيفات

የኢማን መጨመርና መቀነስ, ምስጉን ስነ-ምግባር, የመናገርና የዝምታ ስነ-ስርዓት