إعدادات العرض
አንዲትም አንቀጽ ቢሆን ከኔ አስተላልፉ። ከቤተ እስራኤላውያንም አውሩ ችግር የለውም። ሆን ብሎ በኔ ላይ የዋሸ መቀመጫውን ከእሳት ያመቻች።
አንዲትም አንቀጽ ቢሆን ከኔ አስተላልፉ። ከቤተ እስራኤላውያንም አውሩ ችግር የለውም። ሆን ብሎ በኔ ላይ የዋሸ መቀመጫውን ከእሳት ያመቻች።
ከዐብደሏህ ቢን ዐምር ረዲየሏሁ ዐንሁማ እንደተላለፈው ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦ "አንዲትም አንቀጽ ቢሆን ከኔ አስተላልፉ። ከቤተ እስራኤላውያንም አውሩ ችግር የለውም። ሆን ብሎ በኔ ላይ የዋሸ መቀመጫውን ከእሳት ያመቻች።"
[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪ ዘግበውታል።]
الترجمة
عربي বাংলা Bosanski English Español فارسی Français Bahasa Indonesia Русский Tagalog Türkçe اردو 中文 हिन्दी සිංහල ئۇيغۇرچە Kurdî Hausa Português മലയാളം తెలుగు မြန်မာ Deutsch 日本語 پښتو Tiếng Việt অসমীয়া Shqip Svenska cs ગુજરાતી Yorùbá Nederlands Kiswahili தமிழ் ไทย دری bg ff hu it kn Кыргызча Lietuvių mg or ro rw Soomaali тоҷикӣ uz ak नेपाली mos az woالشرح
ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ከርሳቸው የተማርነውን ቁርአናዊም ይሁን ሐዲሣዊ እውቀት አንድ አንቀፅ ያህል ትንሽ እንኳ ቢሆን እንድናስተላልፈው አዘዙን፤ ይህም ግን የምንጣራበትንና የምናደርሰውን መልእክት ተረድተነው መሆኑ ቅድመ መስፈርቱ ነው። ከዚያም ሽሪዓችን ጋር እስካልተጋጨ ድረስ ከበኒ ኢስራኢሎች የተከሰተባቸውን ክስተትና መሰል ጉዳዮችን በተመለከተ ማውራታችንም ችግር እንደሌለው ገለፁ። ከዚያም በሳቸው ላይ መቅጠፍን አስጠነቀቁ፤ ሆን ብሎ በሳቸው ላይ የዋሸም ጀሀነም ውስጥ ማረፊያውን እንዲይዝ አሳሰቡ።فوائد الحديث
የአላህን ሸሪዓ ማስተላለፍ እንደሚበረታታና ማንኛውም ሰው የሸመደደውና የተረዳውን ትንሽም ቢሆን ማድረስ እንዳለበት፤
አሏህን በትክክል ለማምለክና መልዕክቱንም ለማድረስ እንዲያስችል ሸሪዓዊ እውቀትን መፈለግ ግዴታ መሆኑን፤
ይህ ከባድ ዛቻ ከሚመለከታቸው ሰዎች ላለመሆን ሲባል የትኛውንም ሐዲሥ ከማስተላለፋችንና ከማሰራጨታችን በፊት በትክክል ከሳቸው መሆኑን ማረጋገጥ ግዴታ እንደሆነ፤
ውሸት ላይ ላለመውደቅ ሲባል በተለይም በአሏህ ሸሪዓ ላይ በንግግራችን እውነተኞችና የምናወራውም የተሟላ መረጃው ያለንን ጉዳይ መሆኑ እንደሚበረታታ እንረዳለን።