'አላህ በዳይን ያዘገየዋል። የያዘው ጊዜ ግን አይለቀውም!

'አላህ በዳይን ያዘገየዋል። የያዘው ጊዜ ግን አይለቀውም!

ከአቡ ሙሳ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: "የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል: 'አላህ በዳይን ያዘገየዋል። የያዘው ጊዜ ግን አይለቀውም!'" አቡ ሙሳ እንዲህ አለ: "ቀጥለውም {የጌታህም ቅጣት የከተሞችን ሰዎች እነሱ በዳዮች ሲሆኑ በቀጣቸው ጊዜ እንደዚህ ነው። ቅጣቱ በእርግጥ አሳማሚ ብርቱ ነው።} [ሁድ: 102] የሚለውን አነበቡ።"

[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]

الشرح

ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በወንጀል፣ በሽርክና ሰዎችን በመብታቸው በመበደል ላይ ከመዘውተር አስጠነቀቁ። ምክንያቱም አላህ በዳይን ያዘገየዋል፣ ያቆየዋል ፣ እድሜውንና ገንዘቡንም ያረዝምለታል። በቅጣትም አያቻኩለውም። ካልቶበተ ግፉ ስለበዛ ይይዘዋል አይለቀውምም አይተወውምም። ቀጥለውም ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም {የጌታህም ቅጣት የከተሞችን ሰዎች እነሱ በዳዮች ሲሆኑ በቀጣቸው ጊዜ እንደዚህ ነው። ቅጣቱ በእርግጥ አሳማሚ ብርቱ ነው።} [ሁድ: 102] የሚለውን አነበቡ።

فوائد الحديث

አስተዋይ የሆነ ሰው ወደ ተውበት መቻኮል ይገባዋል። በበደል ላይ የዘወተረ ጊዜ አላህ አዘናግቶ እንደሚይዘው መጠራጠር የለበትም።

አላህ በዳዮችን ማዘግየቱና እነሱን በመቅጣት አለመቻኮሉ እነሱን ማዘናጊያና ካልቶበቱ ቅጣታቸውን ማነባበርያ ነው።

ግፍ የአላህን ቅጣት ህዝቦች ላይ የሚያመጣ አንዱ ምክንያት ነው።

አላህ አንድን መንደር ሲያጠፋ በውስጧ ደጋጎችም ሊኖሩ ይችላሉ። እነዚህ ደጋጎች የትንሳኤ ቀን በሞቱበት መልካምነት ላይ ሆነው ነው የሚቀሰቀሱት። ምድራዊ ቅጣቱ እነሱንም ማካተቱ በመጪው አለም አይጎዳቸውም።

التصنيفات

ዐቂዳ (እምነት), አላህን በስሞቹና በባህሪያቱ መነጠል, ውግዝ ስነ-ምግባር