ሚስቱን ሳይገናኝ እንዲሁም ሳያምፅ ለአሏህ ሐጅ አድርጎ የተመለሰ ልክ እናቱ እንደወለደችበት ቀን (ከወንጀል ንፁህ) ሆኖ ይመለሳል።

ሚስቱን ሳይገናኝ እንዲሁም ሳያምፅ ለአሏህ ሐጅ አድርጎ የተመለሰ ልክ እናቱ እንደወለደችበት ቀን (ከወንጀል ንፁህ) ሆኖ ይመለሳል።

ከአቢ ሁረይራ ረዲየሏሁ ዐንሁ እንደተላለፈው፡ ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ ብሏል፦ "ሚስቱን ሳይገናኝ እንዲሁም ሳያምፅ ለአሏህ ሐጅ አድርጎ የተመለሰ ልክ እናቱ እንደወለደችበት ቀን (ከወንጀል ንፁህ) ሆኖ ይመለሳል።"

[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]

الشرح

ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ሚስቱን ሳይገናኝ - "ረፈሥ" የሚለው ቃል ፆታዊ ግንኙነትንም ይሁን መሳሳምና መተሻሸትን የመሰሉ የግንኙነት መንደርደሪያዎችን እንዲሁም ፀያፍ የቃል አጠቃቀምንም የሚያጠቃልል ቃል ነው። ወንጀልና ኃጢዓት በመፈፀም - ሳያምፅ ‐ ሐጅን ያከናወነ ያለውን ደረጃ ገለፁ። አመጽ ውስጥ ከሚካተቱት መካከል በኢሕራም ጊዜ የተከለከለን ማድረግ ይገኝበታል። በዚህ መልኩ ሐጅን ያከናወነ ሰው ልክ ህፃን ልጅ ከወንጀል የፀዳ ሆኖ እንደሚወለደው እርሱም ከወንጀሉ የተማረ ሆኖ ከሐጅ ይመለሳል።

فوائد الحديث

ወንጀል ምንም እንኳ በማንኛውም ሁኔታ የተከለከለ ቢሆንም የሐጅን የአምልኮ ስርአት ለማላቅ ሲባል በሐጅ ወቅት ክልክልነቱ የበረታ እንደሚሆን፤

የሰው ልጅ ሲወለድ ከወንጀል የፀዳ ሆኖ የሚወለድ በመሆኑ የሌላ ወንጀል የሚጫንበት እንዳልሆነ፤

التصنيفات

የሐጅና ዑምራ ትሩፋት