ግንኙነትና ፆታዊ ስሜትን የሚያነሳሱን ሳይፈፅምና ሳያምፅ ለአሏህ ሐጅ አድርጎ የተመለሰ ልክ እናቱ እንደወለደችው ቀን (ከወንጀል ንፁህ) ሆኖ ይመለሳል።

ግንኙነትና ፆታዊ ስሜትን የሚያነሳሱን ሳይፈፅምና ሳያምፅ ለአሏህ ሐጅ አድርጎ የተመለሰ ልክ እናቱ እንደወለደችው ቀን (ከወንጀል ንፁህ) ሆኖ ይመለሳል።

ከአቡ ሁረይራ ረዲየሏሁ ዐንሁ እንደተላለፈው፡ ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ ብሏል፦ "ግንኙነትና ፆታዊ ስሜትን የሚያነሳሱን ሳይፈፅምና ሳያምፅ ለአሏህ ሐጅ አድርጎ የተመለሰ ልክ እናቱ እንደወለደችው ቀን (ከወንጀል ንፁህ) ሆኖ ይመለሳል።"

[ሶሒሕ ነው።] [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]

الشرح

ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ግንኙነትና ፆታዊ ስሜትን የሚያነሳሱን ያልፈፀመ - "ረፈሥ" የሚለው ቃል ፆታዊ ግንኙነትንም ይሁን መሳሳምና መተሻሸትን የመሰሉ የግንኙነት መንደርደሪያዎችን እንዲሁም ፀያፍ የቃል አጠቃቀምንም የሚያጠቃልል ቃል ነው። ወንጀልና ኃጢዓት በመፈፀም - ሳያምፅ ‐ ሐጅን ያከናወነ ያለውን ደረጃ ገለፁ። አመጽ ውስጥ ከሚካተቱት መካከል በኢሕራም ጊዜ የተከለከለን ማድረግ ይገኝበታል። በዚህ መልኩ ሐጅን ያከናወነ ሰው ልክ ህፃን ልጅ ከወንጀል የፀዳ ሆኖ እንደሚወለደው እርሱም ከወንጀሉ የተማረ ሆኖ ከሐጅ ይመለሳል።

فوائد الحديث

ወንጀል ምንም እንኳ በማንኛውም ሁኔታ የተከለከለ ቢሆንም የሐጅን የአምልኮ ስርአት ለማላቅ ሲባል በሐጅ ወቅት ክልክልነቱ የበረታ እንደሚሆን እንረዳለን።

የሰው ልጅ ሲወለድ ከወንጀል የፀዳ ሆኖ የሚወለድ በመሆኑ የሌላ ሰው ወንጀል የሚጫንበት እንዳልሆነ እንረዳለን።

التصنيفات

የሐጅና ዑምራ ትሩፋት