ቤቶቻችሁን መቃብር አታድርጉ! ቀብሬንም የሚጎበኝ የበአል ስፍራ አታድርጉት! ይልቅ በኔ ላይ ሶለዋት አውርዱ! የትም ብትሆኑ ሶለዋታችሁ ትደርሰኛለችና።

ቤቶቻችሁን መቃብር አታድርጉ! ቀብሬንም የሚጎበኝ የበአል ስፍራ አታድርጉት! ይልቅ በኔ ላይ ሶለዋት አውርዱ! የትም ብትሆኑ ሶለዋታችሁ ትደርሰኛለችና።

አቡ ሁረይራ ረዲየሏሁ ዐንሁ እንዲህ ብለዋል: የአሏህ መልክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል፡ "ቤቶቻችሁን መቃብር አታድርጉ! ቀብሬንም የሚጎበኝ የበአል ስፍራ አታድርጉት! ይልቅ በኔ ላይ ሶለዋት አውርዱ! የትም ብትሆኑ ሶለዋታችሁ ትደርሰኛለችና።"

[ሐሰን ነው።] [አቡዳውድ ዘግበውታል።]

الشرح

ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ቤቶችን እንደ መቃብር ከሶላት የተገለሉ እና ሶላት የማይሰገድባቸው ከማድረግ እየከለከሉ ነው። እንዲሁም ልማድ አድርጎ በመያዝ የሳቸውን ቀብር ደጋግሞ መጎብኘቱንም እዚያው መሰብሰቡም ወደ ሽርክ ስለሚያደርስ ከለከሉ። ከዛ ይልቅ ወደ ቀብራቸው መመላለስ ሳያስፈልግ ቅርብም ይሁን ሩቅ እኩል ለእርሳቸው ስለሚደርሳቸው ከየትኛውም ቦታ ሆነን በሳቸው ላይ ሶለዋት እንድናወርድ አዘዙን።

فوائد الحديث

መኖሪያ ቤቶችን አሏህን ከማምለክ የተራቆቱ ማድረግ ክልክል ነው።

የነቢዩን የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ቀብር ለመዘየር አስቦ ጉዞ መውጣት መከልከሉን እንረዳለን። የዚህም ምክንያት የትም ሆነን ሶለዋት በሳቸው ላይ እንድናወርድ ስላዘዙንና ለርሳቸው እንደሚደርሳቸውም ስለነገሩን ነው። በአምልኮ መንፈስ ጉዞ የሚወጣው ወደ መስጂድ አንነበዊ ለመሄድና እዛው ለመስገድ ከሆነ ብቻ ነው።

በተለየ መልኩና ወቅትን ለይቶ የርሳቸውን ቀብር ደጋግሞ መጎብኘትን ልምድ አድርጎ መያዝ ተከልክሏል። የሌላን ሰው ቀብርም ቢሆን እንደዚሁ የተከለከለ ነው።

የላቀው አሏህ ከየትኛውም ቦታና በማንኛውም ጊዜ በሳቸው ላይ ሶለዋት ማውረድን መደንገጉ ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና አምላካቸው ዘንድ ያላቸውን ከፍተኛ ደረጃ ያሳያል።

መቃብር ዘንድ መስገድ መከልከሉ ሶሓቦች ዘንድ የፀና ጉዳይ በመሆኑ ነቢዩም የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ባልደረቦቻቸው ቤቶቻቸውንም እንደመቃብሩ የማይሰገድበት እንዳያደርጉ ከለከሏቸው።

التصنيفات

የመልካም ስራዎች ትሩፋቶች