ጉዳያችሁ በአንድ መሪ የተሰበሰበ ሁኖ ሳለ አንድነታችሁን ሊሰነጥቅ ወይም ህብረታችሁን ሊበታትን የመጣ ሰውን ግደሉት።

ጉዳያችሁ በአንድ መሪ የተሰበሰበ ሁኖ ሳለ አንድነታችሁን ሊሰነጥቅ ወይም ህብረታችሁን ሊበታትን የመጣ ሰውን ግደሉት።

ከዐርፈጀህ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: "የአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ሲሉ ሰምቻዋለሁ: "ጉዳያችሁ በአንድ መሪ የተሰበሰበ ሁኖ ሳለ አንድነታችሁን ሊሰነጥቅ ወይም ህብረታችሁን ሊበታትን የመጣ ሰውን ግደሉት።"

[ሶሒሕ ነው።] [ሙስሊም ዘግበውታል።]

الشرح

ሙስሊሞች በአንድ መሪና በአንድ ህብረት የተሰበሰቡ ሆነው ሳለ ከዚያም መሪነቱን መገዳደር ፈልጎ ወይም ሙስሊሞችን ከአንድ ህብረት በላይ እንዲሆኑ መበታተን ፈልጎ የመጣን ሰው አደጋውን ለመከላከልና የሙስሊሞችን ደም ለመጠበቅ ሲባል በነርሱ ላይ መከልከልና መጋደል ግዴታ እንደሆነ ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ገለፁ።

فوائد الحديث

ከወንጀል ውጪ በሆኑ ጉዳዮች የሙስሊሞችን መሪ መስማትና መታዘዝ ግዴታ መሆኑን እና በርሱ ላይ አምፆ መውጣትም ክልክል መሆኑን እንረዳለን።

የሙስሊሞች መሪ ላይና ህብረታቸው ላይ አምፆ የወጣ ሰውን ክብሩና ዘሩ ምንም ያህል የላቀ ቢሆን እንኳ እሱን መዋጋት ግዴታ ነው።

በአንድነትና አለመለያየት፣ አለመበታተን ላይ መነሳሳቱን (መበረታታቱን) እንረዳለን።

التصنيفات

በመሪ ላይ ማመፅ