إعدادات العرض
ፊቅህና የፊቂህ መርሆዎች - الصفحة 3
ፊቅህና የፊቂህ መርሆዎች - الصفحة 3
5- ከነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ጋር ነበርኩ። ወደ ቆሻሻ መጣያ ዘንድ ሲደርሱ ቆመው ሸኑ።
16- አንዳችሁ ሰዎች ሰጡትም ከለከሉት ሰዎችን ከሚለምን ይልቅ ገመዱን ይዞ በጀርባው እንጨት አስሮ እያመጣ በመሸጥ አላህ ፊቱን (ከመገረፍ) ቢጠብቅለት የተሻለ ነው።
18- እነዚህ ሁለቱ ከኡመቴ በወንዶቹ ላይ ክልክል ናቸው። ለሴቶቹ ግን የተፈቀደ ነው።
19- አላህና መልክተኛው አስካሪ መጠጥን፣ በክትን፣ አሳማንና ጣዖታትን ከመሸጥ ከልክለዋል።
38- ከሁሉም የክራንቻ ጥርስ ባለቤት አውሬና ከሁሉም ባለጥፍር በራሪ ስጋ (መብላትን) ከልክለዋል።
39- በየሁሉም ሁለት አዛኖች መካከል ሶላት አለ። በየሁሉም ሁለት አዛኖች መካከል ሶላት አለ።" ቀጥለው በሶስተኛው "ለፈለገ ሰው" አሉ።
48- መሳሪያውን በኛ ላይ ያነሳ ከኛ አይደለም።
49- በሩብ ዲናርና ከዛ በላይ በሚያወጣ (ስርቆት) እጅ ይቆረጣል።
50- (አላህን በማመፁ ምክንያት) አላህ ያስቀመጠው የቅጣት ወሰን ካልሆነ በቀር (ስርአት ለማስያዝ) ተብሎ አንድም ሰው ከአስር አለንጋ በላይ እንዳይገረፍ።
51- ከአዳኝ ወይም ከከብት ጠባቂ ውሻ ውጪ የሆነ ውሻን ያሳደገ ሰው በየቀኑ ከስራው ሁለት ቂራጦች ይቀነሱበታል።
52- እኔ የማትጎዳና የማትጠቅም ድንጋይ መሆንህን አውቃለሁ። እኔ ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ሲስሙህ ባላይህ ኖሮ አልስምህም ነበር።
53- ተመለስና ደግመህ ስገድ! አንተ አልሰገድክም።
56- አንተ አቡ ሰዒድ ሆይ! በአላህ ጌትነት፣ በኢስላም ሃይማኖትነት፣ በሙሐመድ ነቢይነት የወደደ ሰው ለርሱ ጀነት ግድ ሆናለታለች።
57- በአላህ መንገድ ላይ አንድ ቀን የጾመ ሰው አላህ ፊቱን ከእሳት ሰባ ዓመታት ያርቀዋል።
58- ሰዎች ማፍጠርን እስካቻኮሉ ድረስ መልካም ላይ ከመሆን አይወገዱም።
62- ሰሑር ተመገቡ! በሰሑር ውስጥ በረከት አለ።
63- ከረመዷን አንድ ቀንም ሆነ ሁለት ቀን በፊት ቀድማቹህ አትፁሙ። ነገር ግን ያስለመደው ጾም የነበረበት ሰው ከሆነ ይፁመው።
65- አንድ ሙስሊም ሴት የአንድ ምሽት መንገድ ከርሷ ጋር የዝምድና ባለቤት የሆነ ወንድ ከሌለ በቀር ልትጓዝ አልተፈቀደላትም።
66- ጾመኛ መሆኑን ረስቶ የበላ ወይም የጠጣ ሰው ጾሙን ይሙላ። ያበላውና ያጠጣው አላህ ነውና።
69- ለይለቱል ቀድርን በረመዷን የመጨረሻ አስር ቀናቶች በጎደሎ ቁጥሮቹ ውስጥ ፈልጓት።
72- የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) በመከራ ወቅት ከምትጮህ፣ ከምትላጭና ልብሷን ከምትቀዳድድ ራሳቸውን አጥርተዋል።
79- አመቱን ሙሉ የጾመ አልጾመም። በወር ሶስት ቀን መጾም አመቱን ሙሉ እንደመጾም ነው።
80- እንዲያ ከሆነ እኔን አታስመስክረኝ! እኔ በበደል ላይ አልመሰክርም።" አሉ።
82- የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) የሴት ልጅ አለባበስን የሚለብስን ወንድና የወንድ ልጅ አለባበስን የምትለብስ ሴትን ረገሙ።
83- ለርሱ (ለኡዱሒያ) የሚታረድ እርድ ያለው ሰው የዙልሒጃ ጨረቃ የወጣች ጊዜ ኡዱሒያውን እስኪያርድ ድረስ ከፀጉሩም ይሁን ከጥፍሩ አንዳችም እንዳይቆርጥ።
84- ረመዳን የገባ ጊዜ የጀነት በሮች ይከፈታሉ፤ የእሳት በሮችም ይዘጋሉ፤ ሰይጣኖችም ይጠፈነጋሉ።
90- ወላሂ አላመነም! ወላሂ አላመነም! ወላሂ አላመነም!" "የአላህ መልክተኛ ሆይ ማን ነው?" ተባሉ። እርሳቸውም "ጎረቤቱ ተንኮሉን ያላመነው ሰው ነው።" አሉ።
